Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አዲሱን አርማ ለሕዝብ ይፋ አደረገ

የካቲት 6 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጲያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ የሚያደርገው ውይይት ከመስከረም 27 እና 28 ቀን 2012 ዓ.ም. በአፍሪካ ህብረት አዳራሽ ከተደረገው የመጀመሪያው የባለድርሻ አካላት ኮንፈረንስ ቀጣይ ሲሆን የውይይቱም ዋና ዓላማ የመጪው አገራዊ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ማድረግ፣ ስለ ምርጫ ቦርዱ የሥራ እንቅስቃሴዎች እና ስለ 2012 አጠቃላይ ምርጫ ዝግጅት መረጃ ማካፈል፣ የምርጫ ዋና ዋና ተሳታፊዎች እና የትብብር ኃላፊነቶች እንዲሁም ስለቦርዱ ሥራዎችን በተመለከተ ውይይት ማድረግ ነው።

Share this post

​​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከካናዳ መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም "የምርጫ ሥራ ድጋፍ ፕሮጄክት" የተሰጠውን ድጋፍ ዛሬ በጋራ ተፈራርሟል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከካናዳ መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም "የምርጫ ሥራ ድጋፍ ፕሮጄክት" የተሰጠውን ድጋፍ ዛሬ በጋራ ተፈራርሟል። በፊርማ ሥነ ስርዓቱ የቦርዱ አመራር አባላት ብዙወርቅ ከተተ እና አበራ ደገፋ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ) ህጋዊ ሰውነት ማጣትን በተመለከተ ውሳኔ ሰጠ

ኢህአዴግ በሊቀመንበሩ በኩል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በላከው ደብዳቤ ግንባሩ መፍረሱን ለቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ሕወሃት) በሊቀመንበሩ በኩል በተጻፈ ደብዳቤ ግንባሩ በመፍረሱ የንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ ቦርዱ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጥያቄ አቅርበዋል። የግንባርን መፍረስ የመወሰን ሥልጣን የቦርዱ በመሆኑ ግንባሩም ሆነ ህወሃት ግንባሩ መፍረሱን መጥቀሳቸው የማይገባ ቢሆንም ቦርዱ ሁለቱ ሊቀመንበራት ያቀረቧቸውን የጽሁፍ ጥያቄዎ መሠረት በማድረግ ግንባሩ መፍረስ አለበት ወይ?

Share this post

ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ

የቦርድ ሰብሳቢ


ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በተለያዩ የመንግስትና የግል ዘርፎች ከ30 ዓመታት በላይ ልምድ ያካበቱ ሲሆን በተለያዩ የአመራር ስፍራዎችም ላይ ሠርተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ከመሾማቸው በፊት ድርጅቱን ለሁለት ዓመታት በዋና ሥራ አስፈፃሚነት ያገለገሉ ሲሆን በ2013 ዓ.ም. በተካሄደው ሀገራዊ ምርጫም ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።

ብዙወርቅ ከተተ

የቦርድ አባል


በ1952 ዓ.ም. የተወለዱት ብዙወርቅ ከተተ፣ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በግሪክ፣ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ደግሞ በኩባ ሐቫና ዩኒቨርሲቲ የውጪ ቋንቋዎች ትምህርት ክፍል በሥነ ቋንቋ የሁለተኛ ደረጃ ዲግሪ አግኝተዋል፡፡

አበራ ደገፋ (ዶ/ር)

የቦርድ አባል


ዶ/ር አበራ ደገፋ፣ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የህግ ተባባሪ ፕሮፌሰር ናቸው፡፡ በህግ የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ዲግሪያቸውን የሠሩት በዚሁ ዩኒቨርሲቲ ሲሆን፣ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን በሶሻል ወርክ እና ሶሻል ዴቨሎፕመንት ከዚሁ ዩኒቨርሲቲ አግኝተዋል፡፡

ውብሸት አየለ

የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ


አቶ ውብሸት አየለ፣ በ1947 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ የተወለዱ ሲሆን፣ በ1980 ዓ.ም. ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በህግ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን አግኝተዋል