Skip to main content

​​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከካናዳ መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም "የምርጫ ሥራ ድጋፍ ፕሮጄክት" የተሰጠውን ድጋፍ ዛሬ በጋራ ተፈራርሟል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከካናዳ መንግሥት ለተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም "የምርጫ ሥራ ድጋፍ ፕሮጄክት" የተሰጠውን ድጋፍ ዛሬ በጋራ ተፈራርሟል። በፊርማ ሥነ ስርዓቱ የቦርዱ አመራር አባላት ብዙወርቅ ከተተ እና አበራ ደገፋ (ዶ/ር) ተገኝተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ) ህጋዊ ሰውነት ማጣትን በተመለከተ ውሳኔ ሰጠ

ኢህአዴግ በሊቀመንበሩ በኩል ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በላከው ደብዳቤ ግንባሩ መፍረሱን ለቦርዱ ያሳወቀ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ሕዝባዊ ወያነ ሐርነት ትግራይ (ሕወሃት) በሊቀመንበሩ በኩል በተጻፈ ደብዳቤ ግንባሩ በመፍረሱ የንብረት ክፍፍልን አስመልክቶ ቦርዱ ውሳኔ እንዲሰጥበት ጥያቄ አቅርበዋል። የግንባርን መፍረስ የመወሰን ሥልጣን የቦርዱ በመሆኑ ግንባሩም ሆነ ህወሃት ግንባሩ መፍረሱን መጥቀሳቸው የማይገባ ቢሆንም ቦርዱ ሁለቱ ሊቀመንበራት ያቀረቧቸውን የጽሁፍ ጥያቄዎ መሠረት በማድረግ ግንባሩ መፍረስ አለበት ወይ?

Share this post

ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ

የቦርድ ሰብሳቢ


ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በተለያዩ የመንግስትና የግል ዘርፎች ከ30 ዓመታት በላይ ልምድ ያካበቱ ሲሆን በተለያዩ የአመራር ስፍራዎችም ላይ ሠርተዋል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ከመሾማቸው በፊት ድርጅቱን ለሁለት ዓመታት በዋና ሥራ አስፈፃሚነት ያገለገሉ ሲሆን በ2013 ዓ.ም. በተካሄደው ሀገራዊ ምርጫም ወሳኝ ሚና ተጫውተዋል።

በቅርቡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ሰርተፍኬትና ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ የሰጣቸው ፓርቲዎች

ጥር 13 ቀን 2012 ዓ.ም.   

በቅርቡ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ሰርተፍኬትና ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ የሰጣቸው ፓርቲዎች የሚከተሉት ናቸው፦

1. ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ፣
2. አንድ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ፣
3. አማራ ጊዮናዊ ንቅናቄ፣
4. እናት ፓርቲ፣

አገው ብሔራዊ ሸንጎ እና ብልጽግና ፓርቲም የሙሉ እውቅና ምዝገባ ፈቃድ ማግኘታቸው ይታወሳል። ጊዜያዊ የምዝገባ ሰርተፍኬት ምንድነው?

Share this post

ጨረታ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ለሚቀጥለው ብሔራዊ ምርጫ በተለያየ መልኩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰጠ ፍቃድ የሚከተሉት አገልግሎትና አቅርቦት ላይ ለመስራት አቅምና ፍላጎት ያላቸው ድርጅቶችን የማሰባሰቢያ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡ በመሆኑም ከስር በሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ዝርዝሩን መመልከት እና ማመልከት ትችላላችሁ፡፡  

ማስታወቂያውን በሪፓርተር፣ በፎርቹን፣ በአዲስ ዘመን እንዲሁም በካፒታል ጋዜጣ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡

ለሚዲያዎች በሙሉ መረጃ ማስተካከያ

ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም.    

የተለያዮ የመንግሥትና የግል ሚዲያዎች የቀጣዮ ብሔራዊ ምርጫ ቀን ሰኔ 21 (June 28) ነው የሚል መረጃ ደርሶናል ትክክል ነው ወይ ብለው ጥያቄ እያቀረቡልን ይገኛሉ። በመሆኑም የሚቀጥለው ምርጫ ቀን ሰኔ 21 (June 28) ነው የሚለው መረጃ ትክክል አለመሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

ለሲዳማ ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች በሙሉ የተላለፈ ጥሪ

ለሲዳማ ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም ላካሄደው ህዝበ ውሳኔ በህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚነት የተሳተፋችሁ በሙሉ የምስክር ወረቀታችሁ ስለተዘጋጀ ሳሪስ ከሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ቅርንጫፍ ከዛሬ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 27 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በስራ ቀንና ሰአት በመገኘት የምስክር ወረቀታችሁን መውሰድ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ