• ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ  e11
    ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የቦርድ ሰብሳቢ
    ሜላትወርቅ ኃይሉ በተለያዩ የመንግሥትና የግል መሥሪያ ቤቶች ከ30 ዓመታት በላይ በማገልገል ልምድ ያላቸው ሲሆን፤ ከባለሞያነት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ አመራርነት ሠርተዋል።
  • ተስፋዬ ንዋይ

    የቦርድ ምክትል ሰብሳቢ


    አቶ ተስፋዬ ነዋይ በመንግሥት ሥራ (በሕዝብ አገልግሎት) ከ17 ዓመታት በላይ ማለትም በዐቃቤ ሕግነት፣ በሰብሳቢ ዳኝነት፣ በሕግ ጉዳዮች ተመራማሪነት እንዲሁም በዩንቨርስቲ መምህርነት አገልግለዋል፡፡ የኢትዮጵያ

  • ፍቅሬ ገ/ሕይወት  e11
    ፍቅሬ ገ/ሕይወት የቦርድ አባል
    ፍቅሬ ገ/ሕይወት ከአምስቱ የቦርዱ ሥራ አመራር አባል አንዱ ሲሆኑ፤ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሕግ እንዲሁም በታሪክ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ አግኝተዋል። ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በልማት ጥናት እንዲሁም በፕሮጀክት አስተዳደር ሠርተዋል።
  • ነሲም አሊ e11
    ነሲም አሊ የቦርድ አባል
    ነሲም አሊ በመንግሥት ሥራ (በሕዝብ አገልግሎት) ለ10 ዓመት ገደማ በተለያዩ የፍርድ ቤት ዕርከኖች በዳኝነት በማገልገል ለሀገራቸው የፍትሕ ሥርዓት ግንባታ ከፍተኛ ሚና ተጫውተዋል፡፡
  • አቶ ተክሊት ይመስል e10
    ተኽሊት ይመሰል የቦርድ አባል
    አቶ ተኽሊት በመንግሥት ሥራ (በሕዝብ አገልግሎት) ከ25 ዓመታት በላይ የካበተ ልምድ አላቸው፡፡ አቶ ተክሊት በነዚኽ ዓመታት የዐቃቤ ሕግ መመሪያ ኃላፊ፣ የከፍተኛ እና የጠቅላይ ፍርድ ቤት ዳኛ፣ የሠበር ሰሚ ችሎት ዋና ሰብሳቢ ዳኛ፣ የዳኞች አስተዳደር ጉባዔ አባል፣ እንዲሁም የከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝደንት ሆነው አገልግለዋል፡፡