Skip to main content

የምርጫ ክርክር ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው የሲቪል ማህበራት እና ሚዲያዎች የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል፣ በዚህም መሰረት የተወሰኑ ተቋማት በተወዳዳሪዎች መካከል የምርጫ ክርክር ለማከናወን ከቦርዱ ፍቃድና አቅጣጫ ለማግኘት ጥያቄዎችን አቅርበዋል።

ይህንን እንዲሁም ሌሎች ልምዶችን መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባ ተጠናቆ ተወዳዳሪ ፓርቲዎች ከታወቁ በኋላ አገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲዎች ክርክርን ለማስተባበር ይፈልጋል። በመሆኑም ከዚህ በፊት ጥያቄ/ ማብራሪያ ያስገባችሁም ሆነ በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት እና ሚዲያዎች በተናጠል ወይም በጋራ የምርጫ ክርክር ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

የፍላጎት መግለጫ ማካተት የሚገባቸው ዋና ዋና ሃሳቦች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአውሮፓ ኅብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የአውሮፓ ሕብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በተገኙበት የተፈጸመው ርክክብ 12 ሃርድ ቶፕ እና 10 ፒክ አፕ መኪኖችን ያካተተ ነው። ዋና ሰብሳቢዋ ቦርዱ የሎጀስቲክ እንቅስቃሴ ላይ ያለበትን ውስንነት ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ቦርዱ በመንግሥትም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት የሚደረጉለት ድጋፎች አስፈላጊነት ገልጸው፤ ለዛም ቦርዱ አመስጋኝ ነው ብለዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎች ምዝግባ እና ተያያዥ የምርጫ ሁነቶችን የተመለከቱ ሪፖርቶችን ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 16 ቀን 2013 ዓ.ም. የ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎች ምዝገባ እና ተያያዥ የምርጫ ሁነቶችን የተመለከቱ ሪፖርቶች ለፖለቲካ ፓርቲዎች የመገናኛ ብዙኃን በተገኙበት አቀረበ። ሪፖርቱ ሦስት አጀንዳዎችን መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ በቅድመ ምርጫ ጊዜ፣ በምርጫው ጊዜና በድኅረ-ምርጫ ጊዜ የሚኖረውን የመረጃ አሰጣጥ ሂደት የተመለከተ ሪፖርት በቦርዱ የመራጮች ትምህርት ክፍል ባልደረባ አማካኝነት ሲቀርብ፤ ቦርዱ የተለያዩ የምርጫ ክልሎች በሚከፍትበት ወቅት ያጋጠሙትን የኦፕሬሽን እና የሎጂስቲክ ፍሰትን የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች በቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባ ቀርቧል።

Share this post

The National Electoral Board of Ethiopia holds discussion with the civic associations licensed for voter education

The National Electoral Board of Ethiopia concluded its two-day discussion with civil society organizations licensed for voter education on Saturday, February, 6, 2021.Deputy Chairperson Woubshet Ayele made an opening remark on the forum which had two sections. While experts presented different countries’ and international experience, Abera Degefa (PhD), Board Member, presented the basic rules of Voter Education Licensing and Ethics Directive No. 4/2012 in relation to the responsibilities of civic associations.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ት/ት ፍቃድ ከተሰጣቸው የሲቪክ ማኅበራት ድርጀቶች ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅዳሜ የካቲት 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ለመራጮች ት/ት ፍቃድ ከተሰጣቸው የሲቪክ ማኅበራት ድርጅቶች ጋር የጀመረውን ውይይት በትላንትናው ዕለት የካቲት 14 ቀን 2013 ዓ.ም.

Share this post

6ተኛ አጠቃላይ ምርጫን መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙሃን- ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖሊቲካ ፓርቲዎች እና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና ቦርዱን ባቋቋመው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ ምርጫውን ለመዘገብ ለሚፈልጉ የመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች ፈቃድ ለመስጠት እና ለመከታተል የሚያስችለውን መመሪያ አርቅቆ፣ የመገናኛ ብዙሃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የስነ ምግባር እና አሰራር መመሪያ ቁጥር 02 /2013 አፅድቋል፡፡

የመገናኛ ብዙሃን ቀጣዩ 6ተኛ አጠቃላይ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሚዛናዊ እና ትክክለኛ እንዲሆን የሚያበረክቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፤የመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ለመዘገብ የሚያስችል የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ይህንን ጥሪ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በዚህ መሠረት ለመዘገብ ጥያቄ የሚያቀርቡ የመገናኛ ብዙሀን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የአሠልጣኞች ሥልጠና ዛሬ ጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም አጠናቋል። ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና በተለያየ ደረጃ ላሉ የIT ባለሞያዎች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የሆነውን ይህን የአሠልጣኞች ሥልጠና በንግግር የከፈቱት የቦርዱ አመራር የሆኑት ፍቅሬ ገብረሕይወት ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሥልጠናውን አስፈላጊነት እንዲሁን ከኮቪድ አንጻር ሊወሰዱ የሚገባቸውን ጥንቃቄዎች አጽንኦት ሰጥተውበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሁለት ረቂቅ መመሪያዎች ላይ ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውይይት ያደረገባቸው ሁለት ረቂቅ መመሪያዎቹ፤ በምርጫ ወቅት የኮቪድ 19 ሥርጭትን ለመቀነስና በምርጫ ሂደት ላይ ሰላምና ፀጥታን የሚያስከብሩ የፀጥታ አስከባሪ አካላት የአሠራር ሥርዓት እና የሥነ-ምግባር ድንጋጌዎችን የያዙ ናቸው። የመጀመሪያው የውይይት መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ጥር 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከጤና ባለሞያዎች፣ ከፓለቲካ ፓርቲዎችና ከፀጥታ አካላት ጋር የተደረገ ሲሆን፤ ቀጣዩና በዛሬው ዕለት ጥር 18 ቀን 2013 ዓ.ም የተደረገው ውይይት ደግሞ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተደርጎ ውሏል።

Share this post