መልስ - ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፓርቲዎች እጩ ለማስመዝገብ ያላቸውን አጭር ጊዜ በመረዳት፣ እንዲሁም በኮቪድ ወረርሽኝ የተነሳ ሊኖር የሚችለውን ንክኪ ለመቀነስ ያቀረቡትንም አቤቱታ መሰረት በማድረግ እጩዎች ለማቅረብ የሚጠበቅባቸውን ፊርማ 6ተኛው አገር አቀፍ ምርጫ ብቻ እንዲታገድ ለተወካዮች ምክር ቤት ጥያቄውን አቅርቧል። አንዳንድ ጠያቂዎች ለፓርቲዎች መስራች ፊርማ የኮቪድ ወረርሽኝን ቦርዱ ለምን ከግምት ውስጥ እንዳላስገባ ሲጠይቁ የነበረ ቢሆንም የመስራች ፊርማ ማሰባሰብ ጊዜ ገደብ የተጠናቀቀው ወረርሽኙ አገራችን ከመግባቱ በፊት በመሆኑ የፓርቲዎች መስራች ፊርማ ማሰባሰብ እና ኮቪድ ወረርሽኝ ግንኙነት እንዳልነበራቸው ማስታወስ ያስፈልጋል።

7