Skip to main content

የመራጮች ትምህርት መሰጠት ለሚፈልጉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የቀረበ ጥሪ

የመራጮች ትምህርት መሰጠት ለሚፈልጉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የቀረበ ጥሪ

ዜጎች በምርጫ ላይ ያላቸውን ትርጉም ያለው ተሳትፎ ለማረጋጋጥ ብሎም ተአማኒነትን ያተረፈ ሰላማዊ ምርጫ ለማድረግ የመራጮች ትምህርት አስፈላጊነት እሙን ነው፡፡ ይህንን አላማ በአገር ደረጃ ለማሳካትም የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ ትልቅ ስፍራ ይይዛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ዓለም አቀፍ ችግር የሆነው የኮሮና ቫይረስ ስጋት በምርጫ ኦፕሬሽን ላይ ስለሚኖረው ተጽእኖ እንዲሁም ሊወሰዱ ስለሚችሉ አማራጭ እርምጃዎች ውይይት አከናውኗል

መጋቢት 11 ቀን 2012 ዓ.ም.

የገዢው ፓርቲን ጨምሮ 45 የፖለቲካ ፓርቲዎች በሁለት የተለያየ ዙር በዚህ ጉዳይ ላይ በተደረገው ውይይት የተሳተፉ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ያለው አገራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ሁኔታ ለጥቂት ሳምንታት እንኳን ከቀጠለ በቀጣይ በዋናነት መፈጸም በሚገባቸው የመራጮች ትምህርት፣ የአስፈጻሚዎች ስልጠና፣ የቁሳቁስ ስርጭት ከፍተኛ የሰው ዝውውርን የሚያሳትፉ በመሆናቸው የመራጮች ምዝገባ ዝግጅት ላይ የሚያደርሰውን ተጽእኖ ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች አቅርቧል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ወረርሽኙ በዚሁ መልኩ ከቀጠለ የምርጫው ዝርዝር አፈጻጸም እና የጊዜ ሰሌዳ ላይ ሊያደርስ የሚችለው ተጽእኖዎችን እና ሊፈጠሩ የሚችሉ ሁኔታዎችን ግምገማ ከፓርቲዎች እና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በተከታታይ እንደሚያደርግ አሳውቋል፡፡ 

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ክልል ካርታን መጋቢት 05 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል

መጋቢት 5 ቀን 2012 ዓ.ም.

ይፋ የማድረጊያ ስነ ስርአቱን በንግግር የከፈቱት ብዙወርቅ ከተተ የቦርዱ አመራር አባል ሲሆኑ ጥሪ የተደረገላቸው የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና የሚዲያ ተወካዮች ተገኝተዋል።

የህግ ባለሙያ ጌታቸው አሰፋ (ዶ/ር) የምርጫ ክልሎች አከላለል እና ህጋዊ ማእቀፍን አስመልክተው በህገ መንግሥቱ ስለተቀመጠው ምርጫ ክልል ምንነት፣ የምርጫ ክልሎችን መወሰኛ መስፈርትና ተያያዥ የህግ ማእቀፎችን አመላክተው ማብራሪያ አቅርበዋል።

Share this post

በምርጫ ሂደት የሚነሱ አለመግባባቶችና ክርክሮች አፈታት ላይ ለፌደራልና ለክልል ፍርድ ቤት ዳኞች ሥልጠና ተሰጠ

 መጋቢት 5  ቀን 2012 ዓ.ም.

አቶ ሰለሞን አረዳ የፌደራል ጠቅላይ ፍ/ቤት ምክትል ሰብሳቢ ፕሮግራሙን የከፈቱ ሲሆን፤ ጌታሁን ካሳ (ዶ/ር) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራር አባል የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና፣ የምርጫ እና የሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/11ን አስመልክተው ሰፋ ያለ ገለጻ አድርገዋል።

ራኬብ አባተ የኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ፎር ኢሌክቶራል ሲስተምስ ካንትሪ ዳይሬክተር የምርጫ ዑደትን እና ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን በተመለከተም ማብራሪያ ሰጥተዋል።

የምርጫ ዑደት እና ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን እንዲሁም አዋጅ ቁጥር 1162/11 ላይ በተሳታፊዎች የቡድን ውይይት እየተደረገ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በምርጫ ጊዜ የሚነሱ አለመግባባቶችና ክርክሮች አፈታትን በማስመልከት አውደ ጥናት አያካሄዱ

የካቲት 28 ቀን 2012 ዓ.ም. 

የአውደ ጥናቱ ዓላማ በመጪው ነሐሴ በሚከናወነው አገር አቀፍ ምርጫ ወቅት ፍርድ ቤቶች የሚኖራቸው ሚና እና የህግ ማእቀፎቹን ማስተዋወቅ እንዲሁም ከዳኞች ጋር ምክክር ማካሔድ ነው፡፡ አውደጥናቱን የከፈቱት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዘዳንት መአዛ አሸናፊ ሲሆኑ በንግግራቸውም የድምፅ ቆጠራ እና የምርጫ ውጤት ጋር የተገናኙ ክርክሮች መጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካል የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት መሆኑን አስታውሰው፣ በምርጫ ሂደቱ ወቅት ለሚኖሩ የፍትህ ሂደቶችም ልዩ የምርጫ ችሎት ማደራጀት ላይ እንደሚሰራ ተናግረዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ፓርቲ (ቅንጅት) መሥራች አባላት ስም ዝርዝርን እንዲያጣራ ለፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ጥያቄ አቀረበ

የካቲት 27 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቀድሞ አዋጅ ተመዝግበው የሚገኙ የፓለቲካ ፓርቲዎች በአዲሱ ህግ ላይ ተቀመጡትን መሥፈርቶች እንዲያሟሉ መጠየቁ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ቅንጅት ለአንድነትና ለዴሞክራሲ በአዲሱ አዋጅ በተደነገገው መሠረት 7,214 (ሰባት ሺህ ሁለት መቶ አስራ አራት) ተጨማሪ መሥራች የፓርቲ አባላትን አስፈርሞ እስከ መጋቢት 3 ቀን 2012 ዓ.ም. ድረስ እንዲያቀርብ ተገልጾለት ነበር። ፓርቲው ጥር 26 ቀን 2012 ዓ.ም. ከ8 ክልሎች የተሰበሰበ የመሥራች አባላት ፊርማ የያዘ ሰነድ ለቦርዱ አቀርቧል። በመሆኑም የቀረበው ሰነድ ላይ የሚከተሉትን ቦርዱ አስተውሏል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓርቲዎች ለቀረቡለት አቤቱታዎች ምላሽ ሰጠ

የካቲት 26 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ፓለቲካ ፓርቲዎች ከመመዝገብ በተጨማሪ የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ሰሞኑን ከተለያዩ ፓርቲዎች የቀረበለትን አቤቱታ አስመልክቶ ምላሾችን ሰጥቷል። በዚህም መሠረት፣ አቤቱታ ያቀረቡ ፓርቲዎች እና ያቀረቧቸው አቤቱታዎች፦

1. ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ትዴፓ/ - እስር፣ ማስፈራራትና ቢሮ መዘጋት፣

2. ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ /ኢዜማ / - ስብሰባዎች መሰናከል፣ በጎንደር በደብረብርሃን እና የጸጥታ ኃይሎች ለመሰናከሉ ትብብር ማድረጋቸው፣

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ጋር ምክክር አካሄደ

የካቲት 19 ቀን 2012 ዓ.ም.                                                                                                          

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አካል ጉዳተኞች በምርጫ ሂደት ስላላቸው ተሳትፎ እንዲሁም ስለ አዲሱ የምርጫ ህግ አካታችነት ከቦርዱ አመራሮችና ሠራተኞች፣ ከክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት የተወጣጡ ሠራተኞች፣ ከኢትዮጵያ አካል ጉዳተኞች ብሔራዊ ማህበራት ፌዴሬሽን (ኢአጉብማፌ) እንዲሁም ከተለያዩ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት ተወካዮች ጋር ምክክር እያካሄደ ይገኛል።
በምክክሩ ከተነሱት ዋና ዋና ሀሳቦች መካከል፦

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመራጮች ትምህርትና ምርጫ መታዘብ ዙሪያ ከተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አከናወነ

የካቲት 7 ቀን 2012 ዓ.ም.       

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመራጮች ትምህርትና ምርጫ መታዘብ ዙሪያ ከተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት እያከናወነ ይገኛል። የውይይቱ ዋና ዋና ዓላማዎች የመራጮች ትምህርት እና ምርጫ መታዘብ ላይ ያለውን ልምድ መዳሰስ፣ የመራጮች ትምህርት ፍቃድ አሰጣጥና የሥነ ምግባር መመሪያ ላይ የተሰጡትን ግብአቶች ማስተዋወቅና ማወያየት፣ የአገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች ፈቃድ አሰጣጥ፣ አሰራርና ሥነ ምግባር መመሪያ ላይ ውይይት ማድረግ ናቸው።

በውይይቱ ላይ የሲቪል ማህበራት ተወካዮች የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን ጨምሮ የተለያዩ የቀድሞ ልምዶቻቸውን ያቀረቡ ሲሆን ይህ ምክክር መድረክ ምርጫ ቦርድ በዚህ ሳምንት ብቻ ካደረጋቸው ውይይት መድረኮች ሶስተኛው ነው።

Share this post

የምርጫ ቦርድ አዲሱ የምርጫ ህግ፣ መመሪያዎች፣ ህጋዊ ማዕቀፍ ነክ ጉዳዮች ለውይይት ቀርበዋል

የካቲት 6 ቀን 2012 ዓ.ም.    

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ መልክ እያከናወነ ያለውን ተቋማዊ ግልጽነትን እና ተአማኒነትን የሚያሳዩ እንዲሁም የተቋም ማንነት ለውጥን የሚወክሉ መገለጫዎችን በማካተት የተቋሙን አዲስ አርማ አዘጋጅቷል። ይህም አርማ የተዘጋጀው የቦርዱን ግልጽነት በሚያሳይ እና አንድ ወጥ የሆነ የተቋም ማንነት ምስል በሚፈጥር መልኩ ነው። የዛሬው ስብሰባ አንዱ ዓላማም ይህንኑ የቦርዱን አዲስ አርማ ለባለድርሻ አካላት እንዲሁም ለሕዝብ ማስተዋወቅ ነው።

Share this post