Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአውሮፓ ኅብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት የካቲት 18 ቀን 2013 ዓ.ም. የአውሮፓ ሕብረትና የጀርመን መንግሥት በጋራ ያበረከቱለትን 22 መኪኖች ተረከበ። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በተገኙበት የተፈጸመው ርክክብ 12 ሃርድ ቶፕ እና 10 ፒክ አፕ መኪኖችን ያካተተ ነው። ዋና ሰብሳቢዋ ቦርዱ የሎጀስቲክ እንቅስቃሴ ላይ ያለበትን ውስንነት ገልጸው ለተደረገው ድጋፍ ያላቸውን ልባዊ ምስጋና አቅርበዋል። ቦርዱ በመንግሥትም ሆነ በአውሮፓ ሕብረት የሚደረጉለት ድጋፎች አስፈላጊነት ገልጸው፤ ለዛም ቦርዱ አመስጋኝ ነው ብለዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎች ምዝግባ እና ተያያዥ የምርጫ ሁነቶችን የተመለከቱ ሪፖርቶችን ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የካቲት 16 ቀን 2013 ዓ.ም. የ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የዕጩዎች ምዝገባ እና ተያያዥ የምርጫ ሁነቶችን የተመለከቱ ሪፖርቶች ለፖለቲካ ፓርቲዎች የመገናኛ ብዙኃን በተገኙበት አቀረበ። ሪፖርቱ ሦስት አጀንዳዎችን መሠረት ያደረገ ሲሆን፤ በቅድመ ምርጫ ጊዜ፣ በምርጫው ጊዜና በድኅረ-ምርጫ ጊዜ የሚኖረውን የመረጃ አሰጣጥ ሂደት የተመለከተ ሪፖርት በቦርዱ የመራጮች ትምህርት ክፍል ባልደረባ አማካኝነት ሲቀርብ፤ ቦርዱ የተለያዩ የምርጫ ክልሎች በሚከፍትበት ወቅት ያጋጠሙትን የኦፕሬሽን እና የሎጂስቲክ ፍሰትን የተመለከቱ ዝርዝር መረጃዎች በቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባ ቀርቧል።

Share this post

The National Electoral Board of Ethiopia holds discussion with the civic associations licensed for voter education

The National Electoral Board of Ethiopia concluded its two-day discussion with civil society organizations licensed for voter education on Saturday, February, 6, 2021.Deputy Chairperson Woubshet Ayele made an opening remark on the forum which had two sections. While experts presented different countries’ and international experience, Abera Degefa (PhD), Board Member, presented the basic rules of Voter Education Licensing and Ethics Directive No. 4/2012 in relation to the responsibilities of civic associations.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ት/ት ፍቃድ ከተሰጣቸው የሲቪክ ማኅበራት ድርጀቶች ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቅዳሜ የካቲት 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ለመራጮች ት/ት ፍቃድ ከተሰጣቸው የሲቪክ ማኅበራት ድርጅቶች ጋር የጀመረውን ውይይት በትላንትናው ዕለት የካቲት 14 ቀን 2013 ዓ.ም.

Share this post

6ተኛ አጠቃላይ ምርጫን መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙሃን- ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖሊቲካ ፓርቲዎች እና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና ቦርዱን ባቋቋመው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ ምርጫውን ለመዘገብ ለሚፈልጉ የመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች ፈቃድ ለመስጠት እና ለመከታተል የሚያስችለውን መመሪያ አርቅቆ፣ የመገናኛ ብዙሃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የስነ ምግባር እና አሰራር መመሪያ ቁጥር 02 /2013 አፅድቋል፡፡

የመገናኛ ብዙሃን ቀጣዩ 6ተኛ አጠቃላይ ምርጫ ፍትሃዊ፣ ሚዛናዊ እና ትክክለኛ እንዲሆን የሚያበረክቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፤የመገናኛ ብዙሃን እና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ለመዘገብ የሚያስችል የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ይህንን ጥሪ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በዚህ መሠረት ለመዘገብ ጥያቄ የሚያቀርቡ የመገናኛ ብዙሀን

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአሠልጣኞች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የአሠልጣኞች ሥልጠና ዛሬ ጥር 27 ቀን 2013 ዓ.ም አጠናቋል። ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና በተለያየ ደረጃ ላሉ የIT ባለሞያዎች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የሆነውን ይህን የአሠልጣኞች ሥልጠና በንግግር የከፈቱት የቦርዱ አመራር የሆኑት ፍቅሬ ገብረሕይወት ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሥልጠናውን አስፈላጊነት እንዲሁን ከኮቪድ አንጻር ሊወሰዱ የሚገባቸውን ጥንቃቄዎች አጽንኦት ሰጥተውበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሁለት ረቂቅ መመሪያዎች ላይ ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውይይት ያደረገባቸው ሁለት ረቂቅ መመሪያዎቹ፤ በምርጫ ወቅት የኮቪድ 19 ሥርጭትን ለመቀነስና በምርጫ ሂደት ላይ ሰላምና ፀጥታን የሚያስከብሩ የፀጥታ አስከባሪ አካላት የአሠራር ሥርዓት እና የሥነ-ምግባር ድንጋጌዎችን የያዙ ናቸው። የመጀመሪያው የውይይት መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ጥር 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከጤና ባለሞያዎች፣ ከፓለቲካ ፓርቲዎችና ከፀጥታ አካላት ጋር የተደረገ ሲሆን፤ ቀጣዩና በዛሬው ዕለት ጥር 18 ቀን 2013 ዓ.ም የተደረገው ውይይት ደግሞ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተደርጎ ውሏል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርት ለማስተማር የእውቅና ጥያቄ ላቀረቡ ሲቪል ማህበራት የመጀመሪያ ዙር እውቅና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርትን ለሚያስተምሩ ሲቪል ማህበራት እውቅና ለመስጠት ባወጣው ጥሪ መሰረት ሲቪል ማህበራት ማመልከቻቸውን ማስገባታቸው ይታወሳል። በዚህም መሰረት የማህበራቱን ማመልከቻዎች በመገምገም እንዲሁም ማሟላት ያለባቸውን ቀሪ ሰነዶች በመጠየቅ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም መሰረት የመጀመሪያ ዙር እውቅና የሰጠ ሲሆን ከስር የተጠቀሱት ድርጅቶች ቦርዱ የሚያቀርብላቸውን ጥያቄዎች አጠናቀው እውቅና የተሰጣቸው ሲቪል ማህበራት ሲሆኑ በማስከተልም ሁለተኛ ዙር እውቅና ሂደት እንደተጠናቀቀ የተጨማሪ ማህበራት እውቅና ይፋ የሚደረግ ይሆናል።

1. ሮሂ ወዱ ላይቭስቶክ ኮምውኒቲ ዴቨሎፐመንት

2. ኢምፐቲ ፎር ላይፍ ዴቨሎፕመንት አሶሲየሽን

3. ቮይስ ፎር ጁስቲስ ኤንድ ዴቨሎፐመንት ኢንተርናሽናል

Share this post

በህጋዊነት ምዝገባ አጠናቃችሁ ጠቅላላ ጉባኤያችሁን እስከ ጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም ማከናወን ለሚጠበቅባችሁ ፓርቲዎች በሙሉ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎችን ምዝገባ ሂደት በሚያከናውንበት ወቅት የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዓ.ም. እና በመመሪያ ቁጥር 3 መሠረት በጠቅላላ ጉባኤ በማድረግ እስከ ጥር 30 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ እንዲያቀርቡ የተገለፀላቸው ፓርቲዎች እንደነበሩ ይታወሳል። ቦርዱ በ2012 ዓ.ም. ሊያካሂድ የነበረው 6ኛ አገራዊ ምርጫ በአለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተውን የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ስጋት ምክንያት ተላልፎ የነበረ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የ6ኛውን አገራዊ ምርጫ የጊዜ ሰሌዳ ይፋ ሆኖ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ ይገኛሉ።

ህጋዊ ምዝገባችሁን ላጠናቀቃችሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አገራዊ ምርጫን ለማከናወን የጊዜ ሰሌዳ ይፋ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ እንዳለ ይታወቃል። በጊዜ ሰሌዳው ላይ ከተጠቀሱት ተግባራት መካከል አንዱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ ምልክት መረጣ ሲሆን በጊዜ ሰሌዳው ላይ ከጥር 13-24 ድረስ የምርጫ ምልክት ማስገቢያ እና መወሰኛ ጊዜ እንደሆነ ተቀምጧል። በዚህም መሰረት የምርጫ ምልክት መረጣው እንደሚከተለው የሚከናወን ይሆናል።

1. የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለምርጫ ምልክትነት ሊሆኑ የሚችሉ የተለያዩ ምልክቶችን ያዘጋጀ ሲሆን የፓርቲ ተወካዮች ከተዘጋጁት ምልክቶች ሊወክለኝ ይችላል የሚሉትን ይመርጣሉ።

2. የመረጡት ምልክት በፓርቲያቸው የተያዘ መሆኑን ያስመዘግባሉ። አንድ ፓርቲ ያስመዘገበው ምልክት ከሚመረጡ ምልክቶች ዝርዝር ውስጥ ይወጣል።