የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በረቂቅ የፓለቲካ ፓርቲዎች የሥርዓተ- ፆታ ኦዲት ሠነድ ላይ የምክክር መድረክ አዘጋጀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት በረቂቅ የፓለቲካ ፓርቲዎች የሥርዓተ- ፆታ ኦዲት ሠነድ ላይ ግብዓት ለመሰባሰብ የሚያስችለውን መድረክ፤ ሁሉም የቦርዱ አመራሮች እንዲሁም የፓለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማኅበራት ተወካዮች በተገኙበት አካሂዷል። መድረኩን በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሠብሳቢ የሆኑት ብርቱካን ሚደቅሳ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ኦዲቱ ያለንበትን የምናውቅበት ብቻ ሣይሆን ለምን እዛ ሆንን ብለን የምንጠይቅበት ጭምር ነው ሲሉ አጽንኦት ሰጥተው ገልጸዋል።