የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ክልል ካርታን መጋቢት 05 ቀን 2012 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል
መጋቢት 5 ቀን 2012 ዓ.ም.
ይፋ የማድረጊያ ስነ ስርአቱን በንግግር የከፈቱት ብዙወርቅ ከተተ የቦርዱ አመራር አባል ሲሆኑ ጥሪ የተደረገላቸው የፓለቲካ ፓርቲዎች፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችና የሚዲያ ተወካዮች ተገኝተዋል።
የህግ ባለሙያ ጌታቸው አሰፋ (ዶ/ር) የምርጫ ክልሎች አከላለል እና ህጋዊ ማእቀፍን አስመልክተው በህገ መንግሥቱ ስለተቀመጠው ምርጫ ክልል ምንነት፣ የምርጫ ክልሎችን መወሰኛ መስፈርትና ተያያዥ የህግ ማእቀፎችን አመላክተው ማብራሪያ አቅርበዋል።
