የውይይት መድረክን ስለመሰረዝ
ጥቅምት 26 ቀን 2012 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን ሲያከናውን ዋና ዋና ከሆኑት የምርጫ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን መራጮች የሚገባውን መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችላቸውን የምርጫ ቅስቀሳ ቀናት አሳውቆ እንደነበር ይታወቃል። ከዚህም በተጨማሪም ለሲቪል ማህበራት እና ለፓርቲዎች ጥሪ በማድረግ አስፈላጊውን የቅስቀሳ መድረክ እንደሚያዘጋጅ ገልጾ እንደነበርም ይታወሳል።