የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርት ለማስተማር የእውቅና ጥያቄ ላቀረቡ ሲቪል ማህበራት የመጀመሪያ ዙር እውቅና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ትምህርትን ለሚያስተምሩ ሲቪል ማህበራት እውቅና ለመስጠት ባወጣው ጥሪ መሰረት ሲቪል ማህበራት ማመልከቻቸውን ማስገባታቸው ይታወሳል። በዚህም መሰረት የማህበራቱን ማመልከቻዎች በመገምገም እንዲሁም ማሟላት ያለባቸውን ቀሪ ሰነዶች በመጠየቅ ሲሰራ ቆይቷል። በዚህም መሰረት የመጀመሪያ ዙር እውቅና የሰጠ ሲሆን ከስር የተጠቀሱት ድርጅቶች ቦርዱ የሚያቀርብላቸውን ጥያቄዎች አጠናቀው እውቅና የተሰጣቸው ሲቪል ማህበራት ሲሆኑ በማስከተልም ሁለተኛ ዙር እውቅና ሂደት እንደተጠናቀቀ የተጨማሪ ማህበራት እውቅና ይፋ የሚደረግ ይሆናል።
1. ሮሂ ወዱ ላይቭስቶክ ኮምውኒቲ ዴቨሎፐመንት
2. ኢምፐቲ ፎር ላይፍ ዴቨሎፕመንት አሶሲየሽን
3. ቮይስ ፎር ጁስቲስ ኤንድ ዴቨሎፐመንት ኢንተርናሽናል