የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የብሔረሰብ ጥናት ኢንስትቲዩት መዛግብትን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ አስረክቧል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኞ ታኅሣሥ 12 ቀን 2013 ዓ.ም የብሔረሰብ ጥናት ኢንስትቲዩት መዛግብትን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጀንሲ አስረክቧል። ቦርዱ በቀድሞው መንግሥት አስተዳደር በመጋቢት 1975 ዓ.ም የተቋቋመውን የብሔረሰቦችን ጉዳይ የሚያጠናውን ተቋም ሠነዶች ወርሶ እንደቆየ የሚታወቅ ሲሆን፤ በወቅቱ በተቋሙ የተሠሩ ጥናቶች አምስት የተለያዩ ዘርፎች ማለትም
• የታሪክ፣ የባሕልና የቋንቋ ጥናት
• የማኅበራዊ ዘርፍ
• የአስተዳደር ጥናት ቡድን
• የኢኮኖሚ ጥናት ቡድን እና
• የሕገ-መንግሥት ጥናት ቡድን ያካተተ ነበር።