ጥያቄ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ ምርጫውን አራዝሟል? የመግለጫው ዋና ሃሳብ ምንድነው?

መልስ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫው ዋና አላማ ምርጫውን ቀድሞ ባቀደው ቀን ማለትም ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ማከናወን እንደማይችል ማሳወቅ ሲሆን፣ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ጥናት አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተጠሪነቱ ለተወካዮች ምክር ቤት ስለሆነ ውሳኔውንም ለተወካዮች ምክር ቤት አሳውቋል፡፡ ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ምርጫውን ማከናወን ካለመቻሉ በስተቀር የተራዘመ ቀን ቆርጦ አላቀረበም፡፡ ቦርዱ ማድረግ የሚችለው አለመቻሉን ብቻ ገልጾ ሪፓርት ለሚያደርግለት ለተወካዮች ምክር ቤት ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡ 
በመግለጫው ተገለጹት የቦርዱ ዋና ዋና ውሳኔዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ 
• በኮቪድ19 የተነሳ ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ምርጫውን ማካሄድ የማይቻለው መሆኑን በመረዳት ያወጣውን የጊዜ ሰሌዳ በመሰረዝ በሰሌዳው መሰረት መከናወን ያለባቸው ተግባራት ለጊዜው እንዲቆሙ ፤

ማስታወቂያ ለፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአገራችን በገባው ኮቪድ19 ወረርሽኝን ተከትሎ የተለያዩ የአሰራር መንገዶችን በመቀየስ ስራውን ለማከናወን ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ የአሰራር ለውጥ የተነሳ እንዲሁም ለሁሉም አካላት ደህንነት ሲባል የተለያዩ ጉዳዮች ያላቸው የፓለቲካ ፓርቲዎችን ጠርቶ ማነጋገርን፣ ውይይት ማድረግንም ሆነ አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠትን አዳጋች አድርጎታል፡፡ 

የሥራ ማስታወቂያ የሚዲያ ክትትል ባለሞያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማቋቋም ላይ ላለው የሚዲያ ክትትል ቡድን (Media monitoring team) የተለያየ ቋንቋ ችሎታ ያላቸው፣ ከሚዲያ ጋር የተገናኘ የሥራ ልምድ ያላቸው ወይም በሚዲያ ክትትልና ሥራ ላይ ያላቸውን ፍላጎት እና ችሎታ በበቂ ሁኔታ ማሳየት የሚችሉ ግለሰቦችን ከአውሮፓ ህብረት የምርጫ ድጋፍ ማእከል ጋር በመተባበር መቅጠር ይፈልጋል፡። 

የሚዲያ ክትትል ባለሞያ የመሆን ፍላጎት ያላችሁ እና መስፈርቱን የምታሟሉ ይህን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማመልከት ትችላላችሁ፡፡ ከአንድ ቋንቋ በላይ ችሎታ ያላቸው አመልካቶች እጅግ በጣም ይበረታታሉ፡፡ 

 

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ