የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን ጋር በመተባበር መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም. በሚደረገው ምርጫ ላይ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች የሚውለውን የነፃ ዐየር ሰዓት ድልድል አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ከኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን ጋር በመተባበር በመጪው መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫ በሚደረግባቸው አካባቢዎች ላይ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች የሚውለውን የነፃ ዐየር ሰዓት ድልድል አካሄደ። የዐየር ሰዓት ድልድሉ መመሪያውን መሠረት አድርጎ፤ በሶማሌ ክልል፣ በሐረሪ ክልል እና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል ለሚወዳደሩ 22 የፖለቲካ ፓርቲዎችና 106 የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች የቀረበ ሲሆን፤ ይህውም በሦስት ሬዲዮ ጣቢያዎች፣ በአራት ቴሌቪዥንና በሁለት ጋዜጦች ላይ ተከናውኗል።