የመራጮች ምዝገባ ሒደት ያልተጀመረባቸው የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መረጃ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ በምዝገባ ሂደቱም ወቅት የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። እንደሚታወቀው የመራጮች ምዝገባ በተወሰኑ ምርጫ ክልሎች መዘግየቱ የሚታወስ ነው። ቦርዱ ከክልል መስተዳድር አካላት ጋር ባደረገው ከፍተኛ የትብብር ስራ የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው የመራጮች ምዝገባ ያልተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባን ለማስጀመር ጥረት ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በዚህም መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከሚያዝያ 29 - ግንቦት 13 ቀን 2013 ድረስ በልዩ ሁኔታ እንዲከናወን ወስኗል።
ከነዚህም መሰረት
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ አጭር መረጃ
የመራጮች ምዝገባን የተመለከተ አጭር ማስታወቂያ
ለአካል ጉዳተኞች አጋዥ የምርጫ ቁሳቁሶች እና ትምህርት መሰጠት ተጀመረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ እንደገና ከተቋቋመበት ጊዜ አንሥቶ በትኩረት እየሠራባቸው ካላቸው ተግባራት አንዱ የአካል ጉዳተኛና የሥርዓተ-ፆታ አካታችነት ተጠቃሽ ናቸው። ይህንንም ይረዳ ዘንድ የምርጫ ሕጉን ማዕቀፎች በዐይነ-ሥውራን ዘንድ ተዳራሽነቱን ለማስፋት ይረዳ ዘንድ ያሳተማቸውን ብሬሎች በአካል ጉዳተኞች የመራጮች ትምህርትና በመታዛቢነት ለተሠማሩ ለሲቪል ማኅበራት መስጠት ጀመረ።
ቦርዱ ብሬሎችን ከመስጠት በተጨማሪ በታዛቢነት ለተሠማሩ ሲቪል ማኅበራት ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚኖራቸው ሕጋዊ እንቅስቃሴ ዕውቅና የሚያስገኝላቸውን ባጅ መስጠት ጀምሯል።
መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፉት ቀናት እንዳሳወቀው በአዲስ አበባ የመራጮች መዝገባ እስከሚያዝያ 29 ቀን 2013 የተራዘመ ሲሆን ያንን ተከትሎ 1500 ሰው በሞላባቸው ቦታዎች ተጨማሪ 32 ምርጫ ጣቢያዎችን ከፍቷል። የምርጫ ጣቢያዎቹ ዝርዝር የሚከተለው ነው። ይመዝገቡ ካርድዎቸን ይውሰዱ።
1. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 16 ወረዳ 05 ም/ጣ/01-01 ንኡስ ጣቢያ
2. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 16 ወረዳ 05 ም/ጣ/03-01 ንኡስ ጣቢያ
3. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 16 ወረዳ 05 ም/ጣ/04 ንኡስ ጣቢያ
4. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 13 ምርጫ ጣቢያ አያት -1 ንኡስ ጣቢያ
5. ቦሌ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 10 ምርጫ ጣቢያ ኮንደሚኒም 4-1
6. ቦሌ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 10 ምርጫ ጣቢያ መሪ ሀ-3 ንኡስ ጣቢያ
7. ቦሌ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 10 ምርጫ ጣቢያ አያት 3 ንኡስ ጣቢያ