ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባን አስመልክቶ የቀረቡ አቤቱታዎች እና የተሰጡ ምላሾች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች በተመዘገቡ እጩዎች ላይ ያላቸውን ቅሬታ እና አቤቱታ ሲቀበል መቆየቱ ይታወሳል። በዚህም መሰረት ዋና ዋናዎቹ ውሳኔ የተሰጠባቸው አቤቱታዎች የሚከተሉት ናቸው።
1. የዎላይታ ብሔራዊ ንቅናቄ በወላይታ ዞን አቃቤ ህግ በእጩነት ተመዝግበዋል ብሎ አቤቱታ የቀረበው ጥያቄ ቦርዱ ተቀብሎ ለብልጽግና ፓርቲ የአቃቤህግነት ስራቸውን መልቀቃቸውን ወይም አቃቤ ህግ መሆን አለመሆናቸውን የሚያሳይ ማስረጃ እንዲያቀርብ ቦርዱ ጠይቋል።
2. የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ብልፅግና ፓርቲ ካቀረባቸው እጩዎች መካከል የክልሉ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ቢሮ ሀላፊ እንደሆኑና ይህም ከሕጉ ጋር እንደሚቃረን በመግለፅ አቤቱታ አቅርበዋል። በዚህም መሰረት ቦርዱ ለብልጽግና ፓርቲ እጩው ስራውን መልቀቅ እንዳለባቸው ወይም እጩነታቸውን መተው እንደሚገባቸው ወስኖ ለፓርቲው አሳውቋል።