የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሚካሄደው ምርጫ ዝግጅት የመስክ ጉብኝት አደረጉ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አመራሮች ከጳግሜ 2 እስከ ጳግሜ 5 ቀን 2013 ዓ.ም. ባሉት ጊዜያት መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫ የሚካሄድባቸውን አካባቢዎች ማለትም ሶማሌ ክልል፣ ሐረሪ ክልል እና ደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል የመስክ ጉብኝት እና ውይይቶችን አከናውነዋል። በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የተመራው ቡድን በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል መቀመጫ ከተማ ላይ የክልሉን ርዕሰ-መስተዳደር፣ የዞን አመራሮችንና በአካባቢው ላይ የሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲ ወኪሎችን አግኝቶ የመስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. ምርጫን የተመለከቱ አጠቃላይ የምክክር መድረክ አካሂዷል። ከድምጽ መስጫ ቀኑ በተጨማሪ በተመሳሳይ መስከረም 20 ለሚካሄደው ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ ውይይት ተደርጓል።