Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥነ ዜጋ ትምህርት ቀጣይነት ዙሪያ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር አካሔደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥነ ዜጋ ትምህርት ቀጣይነት ዙሪያ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች እና ባለድርሻ አካላት ጋር ግንቦት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ምክክር አካሄደ፡፡ በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ንግግር የተከፈተው የምክክር መድረኩ፤ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ተቋማት የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ተሣትፎ ምርጫ በሚደረግባቸው ዓመታት ላይ ብቻ ተወሥኖ እንዳይቀር ግንዛቤ እንዲወሰዱ ለማድረግና በሥነ ዜጋ ትምህርት ቀጣይነት ላይ የቦርዱ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሚና ላይ ግንዛቤ መፍጠር ዐላማው ያደረገ ሲሆን፤ መድረኩ ላይ ከቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ በተጨማሪ የቦርድ አመራር አባል የሆኑት አበራ ደገፋን (ዶ/ር) ጨምሮ የቦርዱ የጽ/ቤት ኃላፊዋ ሜላትወርቅ ኃይሉ ተገኝተውበታል። ከባለድርሻ አካላትም ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በተጨማሪ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተወካዮችና የዘርፉ ባለሞያዎች፤ እንዲሁም የብዙኃን መገናኛ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2013 በጀት ዓመት የመንግሥት ድጋፍ አስመልክቶ የወጣ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 100 ንዑስ አንቀጽ ሁለት በተሰጠው ሥልጣን መሠረት መንግሥት ለፖለቲካ ፓርቲዎች የሚሰጠውን የገንዘብ ድጋፍ ለመወሠን መመሪያ አጽድቆ በሥራ ላይ በማዋል በ2013 በጀት ዓመት በመመሪያው መሠረት በማከፋፈል የፓርቲዎቹን ድርሻ ፓርቲዎቹ በከፈቱት የተለየ የባንክ ሒሣብ ቁጥር ገቢ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

በዚሁ መሠረት ፓርቲዎቹ በባንክ ሒሣብ ቁጥራቸው ገቢ የሆነውን የፋይናንስ ድጋፍ በመመሪያው አንቀጽ 10 መሠረት በአግባቡና ለታለመለት ተግባር ብቻ የፋይናንስ ሕጉን በመከተል በሥራ ላይ በማዋል የበጀት ዓመቱ በተጠናቀቀ በሦስት ወር ጊዜ ውስጥ በተመሰከረለት የውጭ ኦዲተር በማስመርመር በወቅቱ ለቦርዱ ሪፖርት እንዲያቀርቡ ተደንግጓል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ፓርቲዎች የሚያካሄዱትን ጠቅላላ ጉባዔ በተመለከተ የተሰጡ ማብራሪያዎችን ተመልክቶ ተከታዮቹን ውሳኔዎች አሳለፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ፓርቲዎች ከሚያካሄዱት ጠቅላላ ጉባዔ ጋር በተያያዘ ተከታዮቹን ውሳኔዎች አሳልፎ ለፓርቲዎቹ አሳውቋል።

1. የኦጋዴን ብሔራዊ ነፃነት ግንባር/ኦብነግ

የተወሰነበት ቀን፦ ሚያዝያ 28 ቀን 2014 ዓ.ም

ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን ከሚያዝያ 22-24 ቀን 2014 ዓ.ም እንደሚያደርግ ለቦርዱ በመግለጽ የጠቅላላ ጉባዔውን ዝግጅት የሚያሳይ መረጃ መጋቢት 6 ቀን 2014 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ቢያቀርብም፣ በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንቀጽ 8.5 መሠረት ጠቅላላ ጉባዔ እንዲጠራ መወሰን ያለበት የፓርቲው ማዕከላዊ ኮሚቴ በመሆኑ የማዕከላዊ ኮሚቴው ጠቅላላ ጉባዔ እንዲጠራ የወሰነውን ውሳኔ ዝርዝር የሚያሳይ ቃለ ጉባዔ ደብዳቤ በደረሳቸው በ5 ቀን ውስጥ አሟልተው እንዲያቀርቡ ቦርዱ ለፓርቲው ሊቀመንበር በጽሑፍ አሳውቋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ተኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ የተደረገ የግምገማ ውጤት እንዲሁም የተገኙ ትምህርቶችን ማስተዋወቂያ እና ማጠናቀቂያ ዐውደ-ጥናት ዛሬ ሚያዝያ 20 ቀን 2014 ዓ.ም ማካሄድ ጀምሯል፡፡

ቦርዱ የ6ተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ በምርጫ ሂደቱ ላይ ከተገበራቸው የተለያዩ ተግባራት የተገኙ ትምህርቶችን የመሠነድ ተግባር ሲያከናውን የቆየ ሲሆን በሂደቱ የምርጫ ቦርድ አባላት፣ ሠራተኞች፣ የክልል ጽ/ቤት ሃላፊዎች፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ ታዛቢ ቡድኖች፣ የሲቪል ማኅበራት፣ የፊደራል እና የክልል የመንግሥት ባለሥልጣናት፣ የፍትሕ አካላት፣ የፀጥታ እና ሕግ አስከባሪ አካላት በተጨማሪም ከአጋዥ ድርጅቶች የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ፎር ኤሌክቶራል ሲስተምስ (IFES) እና ዩሮፕያን ሴንተር ፎር ኤሌክቶራል ሰፓርት (ECES) በአጠቃላይ ከ400 በላይ ተሳታፊዎች ከተለያዩ የባላድርሻ አካላት በማካተት በየካቲት እና በመጋቢት ወራት ላይ ከ50 በላይ አነስተኛ የቡድን ውይይቶች፣ የምክክር መድረኮች፣ የቃል እና የጽሑፍ መጠይቆች ተከናውነዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ባደረገዉ ማሻሻያ ላይ ቦረዱ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ለቦርዱ ሪፓርት አቅርቧል፡፡ ቦርዱም ፓርቲው ያወጣውን ማሻሻያ ደንብ በመመርመር ያልተሟሉ ጉዳዮች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ውሳኔውን ያሳወቀበት ደብዳቤ ከስር ያገኙታል፡፡

  PDFእዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የሰጠዉ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የቀረቡ አጠራጣሪ ሰነዶችን አስመልክቶ ምርመራ እንዲደረግ ለፌደራል ፓሊስ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ምርመራው ተጣርቶ እስኪጠናቀቅ ፓርቲው በአዋጅ 1162/2011 አንቀፅ 98/3 መሰረት መታገዱን ይገልፃል።

 PDFደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ምክክር ወቅት ይፋ ያደረገው ለፓርቲዎች የሚሰጥ የገንዘብ ድጋፍ መጠን ከስር ይገኛል። የገንዘብ ድጋፉ ከዚህ ቀደም በፀደቀው መመሪያ ላይ በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት የተከናወነ ነው።

 PDFየገንዘብ ድጋፍ መጠን ለማግኘት አዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post