Skip to main content

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ አጭር መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ምርጫ አስፈጻሚዎችን በመቅጠር የምርጫ ስራን እያስፈጸመ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ ሂደት ውስጥ ካጋጠሙት ችግሮች መካከል አንዱ የሆነው የምርጫ አስፈጻሚዎች ክፍያ መዘግየት ነው። በተለያየ ወቅት የተለያዩ ክፍያዎች ሲደረጉ ቢቆዩም ከአስፈጻሚዎች ቅሬታ ሲያስነሳ የነበረ ጉዳይ መሆኑ አልቀረም።

Share this post

የመራጮች ምዝገባን የተመለከተ አጭር ማስታወቂያ

ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ እንደሆነ ይታወቃል፣ በአዋጅ ቁጥር 1162/2011 በተደነገገው መሰረት የመራጮች ምዝገባ በብሔራዊ በአላት ቀናት አይከናወንም። በመሆኑም ነገ ሚያዝያ 22 ቀን 2013 ዓ.ም የስቅለት በአል በመሆኑ፣ ሚያዝያ 23 ቀን 2013 ዓ.ም የሰራተኞች ቀን በመሆኑ እና ሚያዝያ 24 ቀን 2013 ዓ.ም የፋሲካ በአል በመሆኑ ምርጫ ጣቢያዎች ዝግ ሆነው እነደሚውሉ ለማሳወቅ እንወዳለን። ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ሰኞ ሚያዝያ 25

ለአካል ጉዳተኞች አጋዥ የምርጫ ቁሳቁሶች እና ትምህርት መሰጠት ተጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ እንደገና ከተቋቋመበት ጊዜ አንሥቶ በትኩረት እየሠራባቸው ካላቸው ተግባራት አንዱ የአካል ጉዳተኛና የሥርዓተ-ፆታ አካታችነት ተጠቃሽ ናቸው። ይህንንም ይረዳ ዘንድ የምርጫ ሕጉን ማዕቀፎች በዐይነ-ሥውራን ዘንድ ተዳራሽነቱን ለማስፋት ይረዳ ዘንድ ያሳተማቸውን ብሬሎች በአካል ጉዳተኞች የመራጮች ትምህርትና በመታዛቢነት ለተሠማሩ ለሲቪል ማኅበራት መስጠት ጀመረ።

ቦርዱ ብሬሎችን ከመስጠት በተጨማሪ በታዛቢነት ለተሠማሩ ሲቪል ማኅበራት ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ለሚኖራቸው ሕጋዊ እንቅስቃሴ ዕውቅና የሚያስገኝላቸውን ባጅ መስጠት ጀምሯል።

Share this post

መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፉት ቀናት እንዳሳወቀው በአዲስ አበባ የመራጮች መዝገባ እስከሚያዝያ 29 ቀን 2013 የተራዘመ ሲሆን ያንን ተከትሎ 1500 ሰው በሞላባቸው ቦታዎች ተጨማሪ 32 ምርጫ ጣቢያዎችን ከፍቷል። የምርጫ ጣቢያዎቹ ዝርዝር የሚከተለው ነው። ይመዝገቡ ካርድዎቸን ይውሰዱ።

1. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 16 ወረዳ 05 ም/ጣ/01-01 ንኡስ ጣቢያ

2. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 16 ወረዳ 05 ም/ጣ/03-01 ንኡስ ጣቢያ

3. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 16 ወረዳ 05 ም/ጣ/04 ንኡስ ጣቢያ

4. የካ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 13 ምርጫ ጣቢያ አያት -1 ንኡስ ጣቢያ

5. ቦሌ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 10 ምርጫ ጣቢያ ኮንደሚኒም 4-1

6. ቦሌ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 10 ምርጫ ጣቢያ መሪ ሀ-3 ንኡስ ጣቢያ

7. ቦሌ ክ/ከ የምርጫ ክልል 28 ወረዳ 10 ምርጫ ጣቢያ አያት 3 ንኡስ ጣቢያ

Share this post

ከአትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ የተሰጠ አጭር ማሳሰቢያ

በፓርቲዎች ዘንድ አንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምጽ መስጫ ወረቀት ቅደም ተከተልን አጠናቆ ለህትመት ዝግጁ በማድረግ ላይ ይገኛል። በመሆኑም ፓለቲካ ፓርቲዎች ከእጩዎች ጋር የተገናኙ ማንኛውንም አቤቱታዎች በአስቸኳይ ማጠናቀቅ ይኖርበታል።

Share this post