የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ችሎቶች ምሥረታ ሂደት ያለበትን ደረጃና በዚህ ረገድ ከባለድርሻ አካላት የሚጠበቁ የተለያዩ ሚና እና ኃላፊነቶች ላይ ከፍርድ ቤቶች ፕሬዘዳንቶች ጋር ውይይት አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 3 ቀን 2013 ዓ.ም የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ውብሸት አየለና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ሰለሞን አረዳ በተገኙበት ከክልል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶችና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የምርጫ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ችሎቶች ምሥረታ ሂደት ያለበትን ደረጃና በዚህ ረገድ ከባለድርሻ አካላት የሚጠበቁ የተለያዩ ሚና እና ኃላፊነቶች ላይ ውይይት አደረገ። መድረኩ አቶ ውብሸት አየለና አቶ ሰለሞን አረዳ በተከታታይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ አቶ ውብሸት በንግግራቸው የመድረኩን አስፈላጊነት ገልጸው የቦርዱንና የፍርድ ቤቶችን የጋራና የተናጠል ኃላፊነቶች ለያይቶ ማየቱ እንዲሁም የቦርዱን የሥልጣን ኃላፊነት ወሠኑን መረዳት አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። አቶ ሰለሞን አረዳ በበኩላቸው ምርጫ የሕግ የበላይነት መኖሩን ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸው፤ የምርጫን ቅቡልነት ማረጋገጥ የሚቻለው የምርጫውን ፍትሐዊነት ማረጋገጥ ሲቻ