የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሀገር ዐቀፍ ምርጫውን አስመልክቶ በማስተማር ላይ ከተሠማሩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሔሴ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. ሀገር ዐቀፍ ምርጫውን አስመልክቶ በማስተማር ላይ ከተሠማሩ ሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሄደ። የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ፣ የቦርድ አመራር አባል የሆኑት አበራ ደገፋ (ዶ/ር) እና ብዙወርቅ ከተተ፣ እንዲሁም የቦርዱ ፅ/ቤት ሃላፊ ሜላትወርቅ ኃይሉ የተገኙበትን መድረክ የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ባደረጉት ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ማኅበራቱ ለምርጫው ስኬታማነት የነበራቸውን ጉልህ አስተዋጽዖ ጠቅሰው አመስግነዋል።