የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አካሄደ፣ የተለያዩ ውሳኔዎችንም አስተላለፈ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዳር 23 ቀን 2014 ዓ.ም ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር ያደረገ ሲሆን ምክክሩም ፓርቲዎች በማስከተል (ከምርጫ ማግስት) ሊያሟሏቸው ስለሚገባቸው መስፈርቶች፣ ከመንግስት ስለሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ እና እንቅስቃሴዎቻቸው ላይ ስላጋጠማቸው ገደቦች ያካተተ ነበር፣ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሰቢ ብርቱካን ሚደቅሳ እና ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ በተመራው ይህ ውይይት ላይ በቦርዱ ተመዝግበው የሚገኙ የፓለቲካ ፓርቲዎች ተገኝተዋል።
ለፓርቲዎች ከመንግስት ስለተሰጠው ድጋፍ እና ድጋፉን አስመልክቶ ማቅረብ ስለሚገባው ሪፓርት ጥያቄዎችን ያቀረቡ ሲሆን፣ ስለጠቅላላ ጉባኤ እንዲሁም ፓርቲዎች አባላት እና ደጋፊዎቻቸው ላይ ስላጋጠሟቸው ችግሮች ምክክር ተደርጓል።
በመሆኑም ምክክሩን ተከትሎ ቦርዱ የሚከተሉት ውሳኔዎችን አስተላልፏል፤