የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አ.ብ.ን በድጋሜ የሚያካሂደው ጠቅላላ ጉባዔን አስመልክቶ የቀረቡ ሪፖርቶች ላይ ውሣኔ አሣለፈ
የተወሠነበት ቀን ሐምሌ 25 ቀን 2014 ዓ.ም.
የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) መጋቢት 11 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ እና መጋቢት ዘጠኝ እና ዐሥር 2014 ዓ.ም. የተካሄደውን የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባን አስመልክቶ ያቀረበውን ሪፖርት ተከትሎ ቦርዱ ሚያዝያ 13 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ ፓርቲው ከሪፖርቱ ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉና ከመተዳደሪያ ደንቡ አንጻር መርምሮ ያሣለፈው ውሣኔ ሚያዝያ 18 ቀን 2014 ዓ.ም. በቁጥር አ1162/11/586 በተጻፈ ደብዳቤ ለፓርቲው ገልጿል፡፡