የምርጫ ቀን በምስል
ዜጎች በአብዛኛዎቹ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ድምጽ እየሰጡ ሲሆን ከምርጫ ጣቢያዎች የተወሰኑት ይህንን ይመስላሉ
በድምጽ መስጫ ቀን የተከለከሉ ተግባራት ምን ምን ናቸው?
ወደ ምርጫ ጣቢያ የማይገቡ ነገሮች ምንድናቸው?
1. ድምፅ ለመስጠት በተመዘገበችበት የምርጫ ጣቢያ የተገኘች መራጭ፡-
ሀ) የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ ካርድ ያላት፣
ለ) የማንነት ማረጋገጫ መታወቂያ ወይም በመራጮች ምዝገባ ወቅት የተረጋገጠበት ሌላ ሰነድ ያላት፣ወይም ማንነትዋ በምርጫ ምዝገባ ወቅት በምስክሮች ስለመረጋገጡ
በመራጮች መዝገብ ላይ የሰፈረላት፣
ሐ) የመራጮች መዝገብ ላይ ስሟ የሰፈረ፣
መ) ድምፅ ያልሰጠች መሆኑ ሲረጋገጥ ድምጿን የመስጠት መብት አላት
2. የመራጮች ምዝገባ መታወቂያ የጠፋባት መራጭ ጉዳዩን ለምርጫ ጣቢያው በማስረዳት ማንነቷ እንዲሁም በመዝገቡ ላይ ስሟ የሰፈረና ያልመረጠች መሆኑ ሲረጋገጥ ጉዳዩ በቃለ ጉባኤ ተይዞ እንድትመርጥ ይደረጋል፡፡
1. የምርጫ ጣቢያው ሀላፊ አረጋውያን፣ አካል ጉዳተኞችን፣ ነፍሰጡሮችን፣ ጨቅላ ህጻናት የያዙ ወላጆችን፣ መለዮ የለበሱ የመከላከያና የፖሊስ አባላትን ቅድሚያ በመስጠት ድምፅ እንዲሰጡ ማድረግ አለበት
2. በድምፅ አሰጣጡ ሂደት ምልክት ለማድረግና የድምፅ መስጫ ወረቀቱን ወደሳጥን ለመክተት እገዛ የሚያስፈልገው መራጭ ራሱ የመረጠውን ሰው ይዞ የመምጣት መብት አለው
3. በዚህም መሰረት በድጋፍ ፈላጊው የሚመረጥ ሰው :-
ሀ) ዕድሜው 18 ዓመትና ከዚያ በላይ መሆን አለበት
ለ) እጩ ተወዳዳሪ ወይም የእጩ ወኪል መሆን የለበትም
4. አንድ ድጋፍ የሚሰጥ ሰው ከአንድ በላይ መራጭ ለመደገፍ አይችልም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዚህ ደብዳቤ በተገለጸው መሰረት ለሁሉም ደብዳቤ ለደረሳቸው ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች እስከ ነገ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም እኩለ ቀን ድረስ ይህንን ማዘጋጀታቸውን በጽሁፍ እንዲያረጋግጡ እና በደብዳቤ፣ በኢሜይል፣ ወይም በማንኛውም ኤሌክትሮኒክ መንገድ እንዲያሳውቁ ለማሳሰብ ይወዳል።
ለክልል ወይም ለከተማ ም/ቤት መቀመጫ አንድ መራጭ መምረጥ የሚችለው የእጩዎች ብዛት እንደየምርጫ ክልሉ ይለያያል ። አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 1 እጩ፣ እንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 3 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ደግሞ ላይ 9 እጩዎች አንዳንድ የምርጫ ክልሎች ላይ 14 እጩዎች ወይም ሌላ ቁጥር ያለው የመቀመጫ ብዛት ሊኖራቸው ይችላል።
ብዛቱ የሚወሰነው የምርጫ ክልሉ በክልል ም/ቤቱ ባለው የመቀመጫ ቁጥር ብዛት ነው ። በመሆኑም አንድ መራጭ በክልል ም/ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ መምረጥ የሚችለው የዕጩዎች ብዛት በክልል ምክር ቤት ድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ ከላይ ተፅፎ ይገኛል። በዚህም መሰረት አስፈጻሚዎች የድምፅ መስጫ ወረቀት ሲሰጡ ለመራጩ በምርጫ ጣቢያ ውስጥ እስከ ስንት እጩ መምረጥ እንደሚችል ያስረዳሉ።
ሰኞ ሰኔ 14 ቀን ለሚከናውነው አጠቃላይ ምርጫ የፓርቲ ወኪሎችን እውቅና ባጅ የመስጠት ስራ እያከናወናችሁ እንደሆነ ይታወቃል። ካለው አጭር ጊዜ አንጻር የእጩ ወኪሎች ባጅ መስጠትን እስከ ነገ ማታ ሰኔ 13 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ እንድታከናውኑ እናሳስባለን።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኦፕሬሽንስ የስራ ክፍል
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 10 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ