ስለ ጥሞና ወቅት መረጃዎች
የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙሀን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ሀላፊነቶች አሉ፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 በስካይ ላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም
የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙሀን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ሀላፊነቶች አሉ፡፡
የፖለቲካ ፓርቲዎች
በድምጽ መስጫ ቦታ ወይም ከመግቢያው ስፍራ በሚሆኑበት ጊዜ የሚከተሉት ህጎች ሊተገብሩ ይገባል
ለፖለቲካ ፓርቲዎች
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዛሬው ዕለት ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ መረጃዎችን ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:00 ሰዓት ባንቢስ ሱፐር ማርኬት ዐለፍ ብሎ በሚገኘው ዲ-ሊኦፖል ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣
•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል
•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
ሰኔ 08 ቀን 2013 ዓ.ም
የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም እንደሆነ ይታወቃል። በመሆኑም የድምጽ መስጫ ቀን በምርጫ ጣቢያ በመገኘት የሚታዘቡ የፓርቲ ወኪሎቻችሁን እውቅና ለማሰጠት እና ባጅ ለማግኘት በምትወዳደሩበት ምርጫ ክልል ቢሮ በመሄድ ዝርዝራቸውን እንድታስገቡ እናሳውቃለን። ዝርዝር ማስገቢያው ቅጽ እና ቃለመሃላ ፎርም ከዚህ ማስታወቂያ ስር ተያይዟል።
የእጩ ወኪልነት መስፈርቶች
• በእጩ ወኪልነት የሚቀርብ/የምትቀርብ ማንኛውም ሰው የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት አለበት/አለባት።
1. ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሆነ/ች፣
2. እድሜ 21 ዓመት እና ከዚያ በላይ የሆነ/ች፣
3. የመምረጥ እና መመረጥ መብቱ/ቷ በሕግ ያልተገደበ፣
4. የታወቀ ብልሹ ስነ-ምግባር የሌለበት/ባት፣
5. ማንበብ እና መፃፍ የሚችል/የምትችል እና
6. በእጩ ተወዳዳሪነት ያልተመዘገበ/ች መሆን አለበት/ባት፡፡
የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ይህንን ይመስላሉ። ፓለቲካ ፓርቲዎች እና ሲቪል ማህበራት ይህንን የማስተማሪያ ድምጽ መስጫ ወረቀት መጠቀም ትችላላችሁ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር ካከናወነ በኋላ ባደረገው ስብሰባ ከ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ጋር የተያያዙ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።
1. 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን አስቀድሞ እንደተገለጸው በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ በእለቱ ድምጽ መስጠት የማይቻልባቸው አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ጷግሜ 01 ቀን 2013 ዓ.ም ይከናወናል።
እነዚህም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ዛሬ ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም የምክክር መድረክ አከናውኗል። ይህ በተደጋጋሚ ከሚደረጉ የምክክር መድረኮች አንዱ የሆነው ከፓርቲዎች ጋር የሚደረገው ምክክር በዋናነት ቦርዱ የድምጽ መስጫ ወረቀት ህትመትን አስመልክቶ ያጋጠመውን ተግዳሮት ለፓርቲዎች ሪፓርት ያቀረበበት ነው።
የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በሪፓርታቸው እንዳቀረቡት የእጩዎችን ቁጥር መሰረት አድርጎ በተደረገው የገንዘብ ድጋፍ ወቅት ፓርቲዎች የእጩዎች ቁጥር ላይ ባቀረቡት አቤቱታ፣ በማስከተልም በድምጽ መስጫ ወረቀት እና በውጤት ማሳወቂያ ፎርሞች መካከል የማስታረቅ ስራ ሲሰራ የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ላይ የተለያዩ ጉድለቶች መገኘታቸውን አሳውቀዋል። በዚህም መሰረት የቦርዱ ኦፕሬሽን ክፍል ባከናወነው ኦዲት 54 የምርጫ ክልሎች ድምጽ መስጫ ወረቀቶች ድጋሚ ህትመት የሚያስፈልጋቸው ሆነው ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በክስ ሂደት ላያ ያሉ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች
እንዲሁም የተወካዮች ምክር ቤት
ምርጫ ክልል 26 እና 27 በእጩነት ለመወዳደር ጥያቄ አቅርበው እንዳልተቀበለው ይታወቃል።
በዚህም መሰረት መጀመሪያ የምርጫ ክልሎቹ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ፣ በማስከተል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ቀጥሎ ከፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእጩነት ምዝገባ ጥያቄው አግባብ አይደለም ብሎ ሲከራከር እንደነበር ይታወሳል። በዚህም መሰረት ከፍተኛው ፍርድ ቤትም የቦርዱን አሰራር አጽድቆ ነበር።