Skip to main content

ጨረታ

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም ለሚቀጥለው ብሔራዊ ምርጫ በተለያየ መልኩ ድጋፍ እንደሚያደርግ ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰጠ ፍቃድ የሚከተሉት አገልግሎትና አቅርቦት ላይ ለመስራት አቅምና ፍላጎት ያላቸው ድርጅቶችን የማሰባሰቢያ ማስታወቂያ አውጥቷል፡፡ በመሆኑም ከስር በሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ዝርዝሩን መመልከት እና ማመልከት ትችላላችሁ፡፡  

ማስታወቂያውን በሪፓርተር፣ በፎርቹን፣ በአዲስ ዘመን እንዲሁም በካፒታል ጋዜጣ ላይ ማግኘት ይቻላል፡፡

ለሚዲያዎች በሙሉ መረጃ ማስተካከያ

ታኅሣሥ 28 ቀን 2012 ዓ.ም.    

የተለያዮ የመንግሥትና የግል ሚዲያዎች የቀጣዮ ብሔራዊ ምርጫ ቀን ሰኔ 21 (June 28) ነው የሚል መረጃ ደርሶናል ትክክል ነው ወይ ብለው ጥያቄ እያቀረቡልን ይገኛሉ። በመሆኑም የሚቀጥለው ምርጫ ቀን ሰኔ 21 (June 28) ነው የሚለው መረጃ ትክክል አለመሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

ለሲዳማ ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች በሙሉ የተላለፈ ጥሪ

ለሲዳማ ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም ላካሄደው ህዝበ ውሳኔ በህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚነት የተሳተፋችሁ በሙሉ የምስክር ወረቀታችሁ ስለተዘጋጀ ሳሪስ ከሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ቅርንጫፍ ከዛሬ ታህሳስ 20 ቀን 2012 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ታህሳስ 27 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ በስራ ቀንና ሰአት በመገኘት የምስክር ወረቀታችሁን መውሰድ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቦርዱ ተመዝግበው የሚገኙ የአገር አቀፍና የክልል ፓርቲዎች (በአዋጅ ቁ. 1162/2011 መሠረት) ማሟላት ያሉባቸው ግዴታዎች መመርያ አጸደቀ

ታኅሣሥ 27 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ 1162/2011 በተሰጠው ስልጣን መረት የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባን አስመልክቶ ታኅሣሥ 26 ቀን 2011 ዓ.ም. መመሪያ አጽድቋል። መመሪያው ከመጽደቁ በፊት ከፓርቲዎች ጋር የተለያዩ ውይይቶች የተደረጉ ሲሆን ሰባት ፓርቲዎች ደግሞ በጽሁፍ ግብአታቸውን አስገብተዋል። በመመሪያው የተካተቱ ዋና ዋና ጉዳዮች የሚከተሉት ናቸው፦

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፓርቲዎች ምዝገባ ጥያቄዎች ዙሪያ የተለያዩ ውሳኔዎችን አሳለፈ

ታኅሣሥ 16 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ጥያቄ እና፣ የፓርቲ መለያ ሰንደቅ ዓላማ የማጸደቅ ጥያቄን ያቀረቡ ፓርቲዎችን ጉዳይ አይቶ ውሳኔዎችን አሳልፏል በዚህም መሰረት፦

Share this post

የክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች የእጩዎች ማመልከቻ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዋና መስሪያ ቤት ደረጃ የጀመረውን ውስጣዊ አደረጃጀት ሪፎርም በክልል ደረጃ በማስፋት በክልሎች የሚገኙት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶቹን እንደአዲስ እያደራጀ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ከነዚህም መካከል

-የአማራ ክልል የኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ኃላፊ
-የሀረሪ ክልል የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ኃላፊ
-የቤኒሻንጉል ክልል የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ኃላፊ
-የድሬዳዋ ከተማ የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ኃላፊ
ለመመልመል ባወጣው ተደጋጋሚ ማስታወቂያ በቂ ቁጥር ያለው ተወዳዳሪ ሊገኝ ባለመቻሉ የሚከተሉትን መስፈርት የሚያሟሉ አመልካቾች እስከ ታህሳስ 15 ቀን 2012 ዓ.ም ድረስ ማመልከት የሚችሉ መሆኑን ያሳውቃል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለቀጣዮ አገር አቀፍ ምርጫ የመራጮች ምዝገባ ሰነዶች ህትመትና የቁሳቁሶች ግዥ ጀመረ

ታኅሣሥ 9 ቀን 2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለቀጣዩ አገራዊ ምርጫ ከሚያደርጋቸው ዝግጅቶች መካከል አንዱ የሆነውን የመራጮች ምዝገባን ዘመናዊ እና ተአማኒ የሚያደርግ የህትመት ሥራ እንዲጀመር በትላንትናው  ዕለት በዱባይ ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የዚህ የህትመት ውል ዓላማ የምርጫው ሂደት ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀ እና አዲሱ የምርጫ ህግ ላይ የተቀመጡትን መስፈርቶች ያሟላ እንዲሆን፣ ሊፈጠሩ የሚችሉ ስህተቶችን ለመቀነስና እና ማጭበርበርን ለማስወገድ የሚረዳ እንዲሆን እንዲሁም ለምርጫ አስፈጻሚዎች ለመረዳትና ለማስፈጸም ቀላል እንዲሆን ለማድረግ ነው፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሚከተሉት በምዝገባ ሂደት ላይ የነበሩ ፓርቲዎች እውቅና ሰጠ

ታኅሣሥ 2 ቀን 2012 ዓ.ም.

ማብራሪያ

ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ፓርቲዎች እውቅናቸውን ያገኙት በቀድሞው አዋጅ 537/2001 ዓ.ም. መስፈርቱን ጨርሰው አሟልተው ውሳኔ ሲጠብቁ የነበሩ ሲሆን በአዲሱ አዋጅ መሠረት መሟላት ያለበትን መስፈርት እንደማንኛውም ፓርቲ በቦርዱ መመሪያ መሠረት የሚያሟሉ ይሆናል፡፡

Share this post