የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ምርጫ ባልተደረገባቸው ምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት በማድረግ ቀጣዩን የድምፅ መስጫ ቀን ይፋ አድርጓል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ምርጫ ባልተደረገባቸው የምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት አደርጓል። ሁሉም የቦርዱ አመራሮች የተገኙበትን የምክክር መድረክ በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ አማካኝነት ቦርዱ ሲሰራቸው የቆያቸው ስራዎች ሪፓርት ለፓርቲዎች ቀርቧል። በማስከተልም ምርጫ ባልተደረገባቸው አካባቢዎች የሚኖረውን ቀጣይ የምርጫ ሂደት ከአካባቢዎቹ አጠቃላይ ሰላምና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ ዝርዝር መረጃ የተሰጠ ሲሆን፤በቦርዱ ግምገማም ምርጫ ለማድረግ አመቺ ሁኔታ ያለባቸው ቦታዎችም ተለይተው ቀርበዋል። ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ ከግንዛቤ በመክተት ቀጣዩ የድምፅ መስጫ ቀንን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን እንዲሰጡ ተጠይቋል።