Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ምርጫ ባልተደረገባቸው ምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት በማድረግ ቀጣዩን የድምፅ መስጫ ቀን ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 13 ቀን 2013 ዓ.ም. ምርጫ ባልተደረገባቸው የምርጫ ክልሎች ከሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት አደርጓል። ሁሉም የቦርዱ አመራሮች የተገኙበትን የምክክር መድረክ በቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ አማካኝነት ቦርዱ ሲሰራቸው የቆያቸው ስራዎች ሪፓርት ለፓርቲዎች ቀርቧል። በማስከተልም ምርጫ ባልተደረገባቸው አካባቢዎች የሚኖረውን ቀጣይ የምርጫ ሂደት ከአካባቢዎቹ አጠቃላይ ሰላምና ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማገናዘብ ዝርዝር መረጃ የተሰጠ ሲሆን፤በቦርዱ ግምገማም ምርጫ ለማድረግ አመቺ ሁኔታ ያለባቸው ቦታዎችም ተለይተው ቀርበዋል። ያለውን አጠቃላይ ሁኔታ ከግንዛቤ በመክተት ቀጣዩ የድምፅ መስጫ ቀንን ጨምሮ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ፓርቲዎች ሃሳባቸውን እንዲሰጡ ተጠይቋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመራጮች ምዝገባ ባልተደረገቸው እና በተቋረጠባቸው ምርጫ ክልሎችን አስመልክቶ ውሳኔ አስተላለፈ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫን በዋናነት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ያስፈጸመ ሲሆን በመራጮች ምዝገባ ሂደት ላይ በታዪ ጉልህ ግድፈቶች፣ በመራጮች ምዝገባ ላይ በቀረቡ አቤቱታዎችን ለማጣራት ጊዜ በማስፈለጉ እንዲሁም ከጸጥታ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች የተነሳ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም ድምፅ አሰጣጥ ያልተደረገባቸው ቦታዎች እንዳሉ ይታወቃል። በዚህም መሰረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ ቀሪ ምርጫ ያልተከናወነባቸው የምርጫ ክልሎችን፣ የምርጫው ሂደት ያለበትን ሁኔታ እና የመሳሰሉትን በመገምገም የሚከተሉትን ውሳኔዎች አስተላልፏል።

የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የመራጮች ምዝገባ

Share this post

በ6ተኛ አጠቃላይ ምርጫ ባልተደረገባቸው ቀሪ ቦታዎች በአስፈጻሚነት ለመሳተፍ የምትፈልጉ በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም በዋናነት ያስፈጸመ ሲሆን በእለቱ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ላልተከናወነባቸው እና የመራጮች ምዝገባ በድጋሚ ለሚከናወንባቸው ቦታዎች ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቷል። ከነዚህ ስራዎችም መካከል ምርጫ አስፈጻሚዎችን ሁኔታ እና ቁጥር መገምገም አንደኛው ስራ ነው። ምርጫ አስፈጻሚዎች የምርጫ ሂደቱ ዋና አካል መሆናቸውን በመረዳት እና ስራውም ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚጠይቅ በመሆኑ እንዲሁም የምርጫ ሂደቱ ከተጀመረ በኋላ የሰው ሃይል እጥረት እንዳይፈጠር በማሰብ በሶማሌ ክልል፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል እንዲሁም በሐረሪ ክልል ተጨማሪ የሰው ሃይል ምልመላ ማከናወን እንዳለበት አምኗል።

በዚህም መሰረት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተካሄደውን የመራጮች ምዝገባን አስመልክቶ በባለሞያዎች አጣሪ ቡድን አማካኝነት ያካሄደውን የምርመራ ሪፓርት ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቀረበ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. በሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የተካሄደውን የመራጮች ምዝግባን አስመልክቶ በባለሞያዎች የተካሄደውን ምርመራ ለፓርቲዎች እንዲቀርብ አድርጓል። የቦርዱ ሁሉም አመራሮች የተገኙበትን የምክክር መድረክ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ባደረጉት ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ የሰብሳቢዋን ንግግር ተከትሎም በምክትል ሰብሳቢው ውብሸት አየለ አወያይነት በምርምራ ላይ ከተሠማሩት ዘጠኝ ቡድኖች ተወካዮች ቀርበው በየምርጫ ክልሎቹ ያደረጉትን ምርመራ ሂደት፣ ውጤት እና ለቦርዱ የሚያቀርቡትን የውሳኔ ሃሳብ አስረድተዋል። በምርመራ ሂደቱም በቀረቡት ቅሬታዎች ላይ ቀጥተኛ ግንኙነት ካላቸው ግለሰቦች ጋር ባደረጓቸው ቃለመጠይቆች፣ በመሥክ ጉብኝት፣ ከአካባቢው ማኅበረሰብ በሰበሰቧቸው መረጃዎች፣ ከፎቶና ከተንቀሳቃሽ ምስል እንዲሁም ከቀረቡ ከተለያዩ የሠነድ ማስረጃዎችን በመጠቀም ያጠናቀሩትን ሪፖርት አቅርበዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ድምፅ መስጠት ሂደት ጋር ተያይዞ አቤቱታ ካቀረቡ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 22 ቀን 2013 ዓ.ም. በ6ኛው አጠቃላይ ምርጫ ተሣትፈው በድምፅ መስጠት ሂደቱ ላይ አቤቱታ ካቀረቡ ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አድርጓል። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳና የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ በተገኙበት የተከናወነው የምክክር መድረክ፤ በፓርቲዎች የቀረቡ አቤቱታዎችን መፍትሔ ለመስጠት ቦርዱ በሚከተለው ሥርዓት ላይ ካለው ጊዜ አንጻር ፓርቲዎቹ ፈጣንና የተሻለ መፍትሔ ለማግኘት ይረዳል ያሏቸውን የማዳበሪያ ሃሳቦች እንዲያጋሩ ለማስቻል ታስቦ የተዘጋጀ መድረክ ሲሆን፤ ይህንንም የቦርዱ ሰብሳቢና ምክትል ሰብሳቢ በንግግራቸው ገልጸውታል። የቦርዱ የህግ ክፍል ሃላፊም በምክክሩ የተገኙ ሲሆን አቤቱታዎች ሊኖራቸው የሚገባውን ቴክኒካል ይዘት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

Share this post

ማስታወቂያ በ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የተሳተፋችሁ የፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ሂደት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም መከናወኑ ይታወሳል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በእለቱ የፓለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ ዴስክ በማቋቋም በስልክ፣ በአጭር መልእክት፣ በደብዳቤ አቤቱታዎችን ሲቀበል እና በእለቱ መፈታት የሚችሉትን ችግሮችም ሲፈታ መቆየቱ ይታወሳል።>/p>

ቦርዱ ከድምፅ መስጫው ቀን በማስከተል በተለያየ ሁኔታ የቀረቡትን አቤቱታዎች ሲመለከት እና ሲመረምር ቆይቷል። አንዳንዶቹ አቤቱታዎች በየደረጃው በሚከናወነው የምርጫ ሂደት መቅረብ የነበረባቸው እና በምርጫ ክልሎች እና ጣቢያዎች ደረጃ የሚቀርቡ ሲሆኑ ሌሎቹ ደግሞ ቦርዱ በምርመራ የሚያያቸው ናቸው። ቦርዱ ከአቤቱታዎቹ የተቆራረጡ፣ ሙሉ መረጃ ያልያዙ እና መካተት የሚገባውን መረጃዎች ያካተቱ ባለመሆናቸው ምርመራውን አስቸጋሪ መሆኑን ተረድቷል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ የሚዲያ ማብራሪያ ይሰጣል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ሰኔ 17 ቀን 2013 ዓ.ም. እለታዊ የሚዲያ ማብራሪያ ይሰጣል። በመሆኑም ከታች የተጠቀሱትን መሥፈርቶች የምታሟሉ ብዙኃን መገናኛ ከቀኑ 10:30 ስካይላይት ሆቴል ተገኝታችሁ መዘገብ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።

•በኢትዮጵያ ብዙኃን መገናኛ ባለሥልጣን የተመዘገበ የብዙኃን መገናኛ ተቋም መሆን፣

•የቦርዱን ልዩ የዘገባ ባጅ ፊት ለፊት ማንጠልጠል

•ከአንድ ሚዲያ ሁለት ባለሞያዎች (የፎቶ/የቪዲዮ ባለሙያን ጨምሮ) ብቻ መሣተፍ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለክልል እና ለከተማ አሰተዳደሮች የምርጫ ክልል ሃላፊዎች የውጤት ሰነዶቻቸውን ወደማእከል በሚያመጡበት ወቅት ሊሰጣቸው የሚገባውን ትብብር አስመልክቶ ያቀረበው ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ክልል ደረጃ የውጤት ድመራ ተጠናቆ ምርጫ ክልል ሃላፊዎች ወደ ማእከል ሰነዶችን ይዘው እንዲመጡ እንደሚያደርግ ይታወቃል። በመሆኑም የክልል መስተዳድሮች የምርጫ ክልል ሃላፊዎች እና የውጤት ሰነዶቻቸውን ወደማእከል በሚያመጡበት ወቅት ሊሰጣቸው የሚገባውን ትብብር አስመልክቶ ቦርዱ ያቀረበው ደብዳቤ

ደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

መራጭ ዜጎች፣ ለምርጫ አስፈፃሚዎች ፣ ለሚመለከታቸው አካላት በሙሉ

እንደሚታወቀው የ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ድምፅ አሰጣጥ እየተከናወነ ይገኛል።

1, የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዘግይቶ የተጀመረባቸው ቦታዎች በመኖራቸው

2, የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ላይ የቁሳቁስ ስርጭት የዘገየባቸው ቦታዎች በመኖራቸው

3, ድምፅ ለመስጠት ረጅም ሰልፉች ላይ ያሉ ዜጎች በመኖራቸው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት እስከ ምሽቱ 3 ሰአት ድረስ መራዘሙን ቦርዱ ያሳውቃል። በዚህም መሰረት የምርጫ አስፈፃሚዎች እስከ 3 ሰአት ድረስ የሚመጣ ማንኛውንም መራጭ እንዲያስተናግዱ ጥሪ እናስተላልፋለን። ነገር ግን የመራጮች መዝገባቸው ላይ ያሉ ዜጎች መርጠው ያጠናቀቁባቸው እና ለመምረጥ የተሰለፉ ዜጎች በተጠናቀቁበት ቦታዎች የምርጫ ጣቢያ መዝጋት እና የቆጠራ ስራ መጀመር ይችላሉ።

በድምፅ አሰጣት ሂደት ወቅት ችግር ያጋጠማቸው ዜጎች 778 ነጻ የስልክ መስመር በመደወል ማሳወቅ ይችላሉ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ