የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓርቲዎች ለቀረቡለት አቤቱታዎች ምላሽ ሰጠ
የካቲት 26 ቀን 2012 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ በተሰጠው ስልጣን መሠረት ፓለቲካ ፓርቲዎች ከመመዝገብ በተጨማሪ የተለያዩ ድጋፎችን እንደሚያደርግ ይታወቃል። በዚህም መሠረት ሰሞኑን ከተለያዩ ፓርቲዎች የቀረበለትን አቤቱታ አስመልክቶ ምላሾችን ሰጥቷል። በዚህም መሠረት፣ አቤቱታ ያቀረቡ ፓርቲዎች እና ያቀረቧቸው አቤቱታዎች፦
1. ትግራይ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ትዴፓ/ - እስር፣ ማስፈራራትና ቢሮ መዘጋት፣
2. ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ /ኢዜማ / - ስብሰባዎች መሰናከል፣ በጎንደር በደብረብርሃን እና የጸጥታ ኃይሎች ለመሰናከሉ ትብብር ማድረጋቸው፣