Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የመራጮች ምዝገባ ሂደት አፈጻጸምና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶች እንዲሁም መጪ ሁነቶችን የተመለከተ ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 7 ቀን 2013 ዓ.ም ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የመራጮች ምዝገባ ሂደት አፈጻጸምና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን እንዲሁም ቀጣይ የምርጫ ተግባራትን የተመለከተ ብዙኃን መገናኛ አካላት በተገኙበት ውይይት አካሂዷል። የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተከፈተው መድረክ የድምፅ መስጫ ወረቀት ኅትመት፣ የሎጀስቲክ ማጓጓዝ፣ የመራጮች ምዝገባ ሂደትና የተለያዩ ተግዳሮቶች ከነተሰጡባቸው መፍትሔዎች ጭምር ቀርበውበታል። በሎጀስቲክ ማጓጓዝ ወቅት የተፈጠሩ መስተጓጎሎች፣ በአንዳንድ አካባቢዎች የተስተዋሉ የምርጫ ጣቢያዎች በጊዜ አለመከፈትና የተከፈቱት ሲሞሉም በአፋጣኝ ንዑስ ጣቢያዎችን ለመክፈት ከክልልና ከከተማ መስተዳደሮች ጋር በመነጋገር መፍትሔ ለመስጠት እንደተሞከረ ሆኖም ግን በሚፈለገው ፍጥነት ቦታዎቹን ማግኘቱ ቀላል እንዳልነበረ ተገልጿል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምፅ መስጫ ወረቀት የኅትመት ሂደትንና የደኅንነት አጠባበቅ ሥርዓቱን ለፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች አስጎበኘ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች እና ሚዲያዎች የተወጣጣ የልኡካን ቡድን ወደደቡብ አፍሪካ በመላክ የድምጽ መስጫ ወረቀት ህትመትን እንዲጎበኙ አደረገ። በቦርዱ ከፍተኛ አመራር ፍቅሬ ገብረ ሕይወት ለተመሩት ከፓርቲዎች እና ከሚዲያዎች ለተውጣጡ ተወካዮች የድምፅ መስጫ ወረቀት የኅትመት ሂደቱን፣ የቴክኒክና የደኅንነት አጠባበቅ ሥርዓቱን በዝርዝር ማሳየት ችሏል። ቦርዱ የፍትሐዊ አሠራሩ አንዱ ማሳያ አድርጎ ከሚወስደው የድምፅ መስጫ ወረቀት የዕጩዎች አደራደር ቅደም ተከተል መወሠኛ ሎተሪን በይፋ ካስጀመረበት ከመጋቢት 25 ቀን 2013 ዓ.ም. ጀምሮ የድምፅ መስጫ ወረቀት ኅትመቱ የተጀመረ ሲሆን፤ ይህንንም ሥራ ከሚያካሂዱት ሁለት የኅትመት ድርጅቶች አንዱ በሆነውና በደቡብ አፍሪካ የሚገኘውን የሬን-ፎርም ኅትመት ማኅበር ከፓርቲዎች እና ከሚዲያዎች የተወጣጡ የታዛቢ ቡድኑ አባላት ጎብኝተውታል።

Share this post

የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቃል

በመላው አገሪቱ በ11 ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች ሲካሄድ የቆየው የመራጮች ምዝገባ ዛሬ ይጠናቀቃል። በመሆኑም በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር፣ በአፋር ክልል፣በአማራ ክልል፣ በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል፣ በድሬዳዋ ከተማ መስተዳድር፣ በሃረሪ ክልል፣ በኦሮሚያ ክልል፣ በጋምቤላ ክልል ፣ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ክልል, በሲዳማ ክልል እንዲሁም ሶማሌ ክልል የድምጽ መስጫ ካርድ የመውሰጃ የመጨረሻ ቀን ዛሬ በመሆኑ ድምጽ መስጫ ካርድ ያልወሰዳችሁ ዜጎች እንድትወስዱ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

ለዜጎች መረጃ የምታቀርቡ ሚዲያዎች፣ ማህበራዊ ሚዲያ ተሳታፊዎች እና የፓለቲካ ፓርቲዎች እጩዎች የምዝገባ የመጨረሻው ቀን ዛሬ መሆኑን በማስታወስ ዜጎች ካርዳቸውን እንዲወስዱ እንድታበረታቱ እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ግንቦት 06 ቀን 2013 ዓ.ም

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በየደረጃው ለሚገኙ አስፈጻሚዎች የስራ ዉል በተመለከተ የፃፈዉ ደብዳቤ

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር የስራ ውል ያላችሁ በየደረጃው የምትገኙ አስፈጻሚዎች የስራ ውላችሁ መራዘሙን የሚያሳየው ደብዳቤ ከስር የተያያዘ ሲሆን ለየምርጫ ክልሎቹ እና ዞን አስተባባሪዎች የተላከው ይህ ደብዳቤ እንደ ህጋዊ ሰነድ የሚቆጠር መሆኑን እናሳውቃለን።

ደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ ለአይ.ሲ.ቲ ቲም ሊደሮች       ለምርጫ ጣቢያ የምርጫ አስፈፃሚዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ያለውን የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች በተመለከተ የሰጠዉ ተጨማሪ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር በጋራ መኖሪያ ቤቶች አካባቢ ያለውን የመራጮች ምዝገባ ጣቢያዎች እጥረት ለማስተካከል እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ከቅዳሜ ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተጨማሪ ጣቢያዎች በመክፈት የቀሩት የመራጮች ምዝገባ ቀናት የተሻለ ምዝገባ እንዲካሄድ ጥረት እያደረገ ይገኛል።

በመሆኑም በዚህ መሰረት ከስር በሚገኙት ዝርዝር አድረሻዎች መራጮች ምዝገባ ማከናውን እንደሚችሉ እየገለጽን ችግሮችን ሪፓርት ለማድረግ በነጻ የስልክ መስመራችን 778 በመደወል እንድታሳውቁን እንጠይቃለን።

በልዩ ሁኔታ በተለይ በጀሞ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ምርጫ ጣቢያዎችን ለመክፈት ለከተማ መስተዳድሩ በተደጋጋሚ ብናሳውቅም ከወረዳው ቢሮዎችን ማዘጋጀት ባለመቻሉ ከታቀዱት 15 አዳዲስ ጣቢያዎች 6ቱ መከፈት አልቻሉም። ይህንን ከወረዳው ያጋጠመንን ችግር ለመፍታት እየሰራን እንገኛለን።

Share this post

አጭር መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። የመጀመሪያዎቹ ቀናት ላይ የነበረው ዝቅተኛ የመራጮች ምዝገባ ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ መሻሻል ከማሳየቱም በላይ መራጮች በተለይ የምዝገባው ማጠናቀቂያ ቀናት ሲቃረቡ በከፍተኛ ሁኔታ እየተመዘገቡ እንደሆነ ይታወቃል።

ይህንን ተከትሎ በተለይ በአዲስ አበባ ከተማ የጋራ መኖርያ ቤቶች አካባቢ ከፍተኛ ሰልፍ፣ የመራጮች ፍላጎት እና የምርጫ ጣቢያዎች አለመመጣጠን ተስተውሏል በመሆኑም ካለፈው ሳምንት አንስቶ ቦርዱ በልዩ ሁኔታ ችግሩን ለመፍታት እየሰራ ይህንን ተከትሎ የሚወስዳቸውን እርምጃዎቹን የሚያሳውቅ ይሆናል። በመሆኑም ለተፈጠረው የዜጎች መጉላላት ከፍተኛ ይቅርታ እየጠየቅን እርምጃዎቹን እስኪያሳውቅ ዜጎች እና አስፈጻሚዎች በትእግስት እንዲጠብቁን እናሳውቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባን አስመልክቶ የተሰጠ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእጩዎች ምዝገባ ከተጠናቀቀበት ጊዜ ጀምሮ የሚቀርቡ አቤቱታዎችን በመቀበል፣ ችግሮችን በመፍታት እንዲሁም የድምጽ መስጫ ወረቀት ቅደም ተከተል ሎተሪን በማከናወን የእጩዎችን ዝርዝር አጠናቆ ለድምጽ መስጫ ወረቀት ህትመት ሲያዘጋጅ ቆይቷል።

በምርጫ በፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ስነምግባር አዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 39 (3) የፖለቲካ ፓርቲ እጩውን መለወጥ ወይም መተካት የሚቻልበት ቀን የእጩ ምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ ካለቀ በኋላ ከሆነ ከድምጽ መስጫው ቀን ከአንድ ወር በፊት ባለው ጊዜ ውስጥ ብቻ እንደሆነ ይደነግጋል። በዚህም መሰረት ከዛሬ ከሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ የእጩ መተካት፣ መቀየር፣ መለወጥ እና ማንኛውንም አይነት ማሻሻያ የማይቀበል መሆኑን ይገልጻል።

Share this post

የመራጮች ምዝገባ ሒደት ያልተጀመረባቸው የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ በምዝገባ ሂደቱም ወቅት የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። እንደሚታወቀው የመራጮች ምዝገባ በተወሰኑ ምርጫ ክልሎች መዘግየቱ የሚታወስ ነው። ቦርዱ ከክልል መስተዳድር አካላት ጋር ባደረገው ከፍተኛ የትብብር ስራ የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው የመራጮች ምዝገባ ያልተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባን ለማስጀመር ጥረት ሲያደርግ የቆየ

Share this post

የመራጮች ምዝገባ ሒደት ያልተጀመረባቸው የምርጫ ክልሎችን በተመለከተ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተሰጠ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ የመራጮች ምዝገባን እያከናወነ እንደሆነ በምዝገባ ሂደቱም ወቅት የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት እየሰራ እንደሆነ ይታወቃል። እንደሚታወቀው የመራጮች ምዝገባ በተወሰኑ ምርጫ ክልሎች መዘግየቱ የሚታወስ ነው። ቦርዱ ከክልል መስተዳድር አካላት ጋር ባደረገው ከፍተኛ የትብብር ስራ የምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው የመራጮች ምዝገባ ያልተጀመረባቸው ቦታዎች የመራጮች ምዝገባን ለማስጀመር ጥረት ሲያደርግ የቆየ ሲሆን በዚህም መሰረት የመራጮች ምዝገባ ከሚያዝያ 29 - ግንቦት 13 ቀን 2013 ድረስ በልዩ ሁኔታ እንዲከናወን ወስኗል።

ከነዚህም መሰረት

Share this post