የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ፓርቲዎች ያቀረቡትን የምዝገባ ፍቃድ አስመልክቶ ተከታዩን ውሣኔ አሣልፏል
1. በእነአቶ መንግሥቱ ዩንካ ላይ
የተወሠነበት ቀን ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም.
ሰኔ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሠረት “የሲዳማ አርነት ግንባር (ሲአግ)” በሚል ስያሜ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲነት ጊዜያዊ የምዝገባ ፈቃድ እንዲሰጠው ለቦርዱ አመልክተዋል።
ምርጫ ቦርድ ሐምሌ 13 ቀን 2014 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ እነአቶ መንግሥቱ ዩንካ ያቀረቡትን የጊዜያዊ ዕውቅና ጥያቄ መርምሯል። በዐዋጁ አንቀጽ 86/1 የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ ስያሜ ከተመሳሳይ የፖለቲካ ፓርቲ ስም ጋር የማይመሳሰል ወይም በመራጮች ዘንድ መደናገር የማይፈጥር የፓርቲው ብቸኛ መጠሪያ መሆን እንዳለበት ተደንግጓል።