Skip to main content

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበር በቦርዱ የክልል ጽ/ቤቶች የሚሰሩ የተባበሩት መንግስታት በጎ ፍቃደኞች ስልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 4 ቀን 2013 ዓ.ም የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ብርቱካን ሚደቅሳና የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ በተገኙበት ለሁለት ቀናት የሚቆየውን የተባበሩት መንግሥታት የበጎ ፍቃደኞች ሥልጠና አስጀምረዋል። የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች ላይ የሚኖረውን የሥራ ሂደት ቀልጣፋና ዘመናዊ አፈጻጸም እንዲኖረው ለማስቻል ታስቦ ከተባበሩት መንግስታት በጎ ፍቃደኝነት ተቋም ጋር በመተባበር በጎ ፍቃደኞች የተመለመሉ ሲሆን በዛሬው እለት የተዘጋጀላቸው የስልጠና መርሃ ግብርን የቦርዱ ሰብሳቢ ከፍተውታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ችሎቶች ምሥረታ ሂደት ያለበትን ደረጃና በዚህ ረገድ ከባለድርሻ አካላት የሚጠበቁ የተለያዩ ሚና እና ኃላፊነቶች ላይ ከፍርድ ቤቶች ፕሬዘዳንቶች ጋር ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 3 ቀን 2013 ዓ.ም የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ውብሸት አየለና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት አቶ ሰለሞን አረዳ በተገኙበት ከክልል ፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንቶችና ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር የምርጫ ጉዳዮችን የሚመለከቱ ችሎቶች ምሥረታ ሂደት ያለበትን ደረጃና በዚህ ረገድ ከባለድርሻ አካላት የሚጠበቁ የተለያዩ ሚና እና ኃላፊነቶች ላይ ውይይት አደረገ። መድረኩ አቶ ውብሸት አየለና አቶ ሰለሞን አረዳ በተከታታይ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን፤ አቶ ውብሸት በንግግራቸው የመድረኩን አስፈላጊነት ገልጸው የቦርዱንና የፍርድ ቤቶችን የጋራና የተናጠል ኃላፊነቶች ለያይቶ ማየቱ እንዲሁም የቦርዱን የሥልጣን ኃላፊነት ወሠኑን መረዳት አስፈላጊ መሆኑን አስረድተዋል። አቶ ሰለሞን አረዳ በበኩላቸው ምርጫ የሕግ የበላይነት መኖሩን ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸው፤ የምርጫን ቅቡልነት ማረጋገጥ የሚቻለው የምርጫውን ፍትሐዊነት ማረጋገጥ ሲቻ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ተኛውን አገር አቀፍ የመጨረሻ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በታኅሣሥ 16 ቀን 2013 ዓ.ም የቦርዱ አመራሮችና ፖለቲካ ፓርቲዎች በተገኙበት የመጪው አገር አቀፍ ምርጫን ጊዜያዊ የጊዜ ሰሌዳ ለውይይት እንዳቀረበ ይታወሳል። በእለቱም ፓለቲካ ፓርቲዎች ጥያቄዎችን እና አስተያየቶችን ያቀረቡ ሲሆን ቦርዱም እጩዎችን ለማቅረብ የሚያስፈልገውን ፊርማ የህግ መስፈርት ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ብቻ አገልግሎት ላይ እንዳይውል የተወካዮች ምክር ቤትን መጠየቁ ይታወሳል። በዚሀም መሰረት የመጨረሻው የጊዜ ሰሌዳ እንደሚከተለው ይፋ ሆኗል። ብሔራዊ ምርጫ ቦርድም በዚሁ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ተግባራቱ አፈጻጸም ያሉበትን ሁኔታ የሚያሳውቅ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

ጥያቄ - የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ ለምን ከምርጫው በፊት አልተደረገም?

መልስ - የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ ከምርጫው ጋር መደረጉ የህዝበ ውሳኔውን ኦፕሬሽን በጣም ቀላል የሚያደርገው ሲሆን ከፍተኛ ወጪንም የሚቀንስ ይሆናል፡፡ ቦርዱ ለብሔራዊ ምርጫ እየተዘጋጀ ቀድሞ ህዝበ ውሳኔ ለማደራጀት በቂ ጊዜ የማይኖረው ሲሆን ከዚያም

ጥያቄ - ከድጋሚ ድምጽ መስጠት ጋር የተያያዙ ስጋቶች እንዴት ይታያሉ?

መልስ - አንድ ሰው አንድ ቦታ በመራጭነት ለመመዝገብ በምርጫ ጣቢያው ነዋሪነቱን ተረጋግጦ ሲሆን መስፈርቱን አሟልቶ ለመመዝገቡ ደግሞ የመራጭነት መታወቂያ መያዝ አለበት። በአካባቢው ነዋሪ ያልሆነ መራጭ ተመዝግቧል የሚል ጥርጣሬ ካለ የመራጮች ምዝገባ መዝገብ በየምርጫ ጣቢ

ጥያቄ - የአዲስ አበባና የድሬዳዋ መስተዳደር ድምፅ መስጫ ቀን በተለያየ ቀን መሆኑ ምን ጥቅም አለው?

መልስ - ምርጫ አስፈጻሚዎች ለአንድ ምርጫ ክልል (constituency) ብቻ ደምረው ሪፓርት ያደርጋሉ፣ ይህም የውጤት ስህትት እንዳይፈጠር ያደርጋል፤ ድምፅ ሰጪዎች ያለምንም መምታታት ድምፅ መስጠት ይችላሉ፤ የምርጫ ታዛቢዎች ጋዜጠኞች እንዲሁም የፓርቲ ወኪሎች አዲስ አበባ እና

ጥያቄ - የአዲስ አበባና የድሬዳዋ መስተዳደር ድምጽ አሰጣጥ እና ቆጠራው በአንድ ቀን ቢደረግ ችግሩ ምንድነው?

መልስ - ድምጽ ሰጪዎች ድምጽ የሚሰጡበት የምርጫ ክልሎች የተለያዩ በመሆናቸው በድምጽ አሰጣጥ ወቅት መምታታትን ያስከትላል፤ ምርጫ አስፈጻሚዎች ውጤት ቆጥረው ወደሚመለከተው የምርጫ ክልል የሚልኩ ሲሆን በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ግን ለሁለት እና ለሶስት ምርጫ ክልሎች ውጤትን አከፋፍለው እንዲልኩ ይገደዳሉ ይህም በውጤቱ ድመራ ላይ መምታታት ሊያመጣ ይችላል፣ የምርጫውን አፈጻጸምም አስቸጋሪ ያደርገዋል፤ ምርጫ አስፈጻሚዎች ለተለያዩ የምርጫ ክልሎች ውጤትን በታትነው እንዲልኩ የተለየ የቆጠራ እና የውጤት ሪፓርት አደራረግ ስልጠና ማግኘት ይኖርባቸዋል ይህም ተጨማሪ የኦፕሬሽን ጫና ከመሆኑም በላይ ለዚህ የተለየ ህትመቶችን የማዘጋጀት ተጨማሪ ጫና ያስከትላል።