Skip to main content

ከአትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ የተሰጠ አጭር ማሳሰቢያ

በፓርቲዎች ዘንድ አንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምጽ መስጫ ወረቀት ቅደም ተከተልን አጠናቆ ለህትመት ዝግጁ በማድረግ ላይ ይገኛል። በመሆኑም ፓለቲካ ፓርቲዎች ከእጩዎች ጋር የተገናኙ ማንኛውንም አቤቱታዎች በአስቸኳይ ማጠናቀቅ ይኖርበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመረጮች ምዝገባና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን አስመልክቶ ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች ሪፓርት አቀረበ

መድረኩን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የመሩት ሲሆን፤ ምርጫ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን የሚያሣትፍ መድረክ እንደሆነና ከባለድርሻ አካላቱ መካከልም ፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ እንደመሆናቸው መጠን ስሕተቱንም ስኬቱንም እንዲያውቁ በማድረግ እየተራረሙ ለመሄድ በተከታታይ እየተዘጋጁ ያሉት መድረኮችን ማዘጋጀት እንዳስፈለገ ገልጸዋል። የሰብሳቢዋን ንግግር ተከትሎ የቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረቦች ለምርጫ ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች የግዢ አፈጻጸም፤ ሥርጭትና የሰው ኃይል ሥምሪትን፣ የቁሳቁሶች ጥራትና ደኅንነት አጠባበቅን፣ እንዲሁም ከምርጫ ጣቢያዎች አከፋፈት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ማመልከቻ ላስገቡ እና በመጀመሪያ ዙር ላለፉ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት ቀናት ማለትም የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. እና የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. 6ኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ማመልከቻ ላስገቡ እና በመጀመሪያ ዙር ላለፉ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሥልጠና ሰጠ። በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ የተከፈተው መድረክ የተለያዩ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ በቦርዱ የፕሮግራም ባለሙያ-የውጭ ግንኙነት ክፍል፣ በቦርዱ የሥርዓተ -ፆታ እና አካታችነት ክፍል እንዲሁም ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮ ባላቸው ባለሙያ ቀርቧል። ሥልጠናውን ለምን መስጠት እንዳስፈለገ የተናገሩት የቦርድ አመራሯ ብዙወርቅ ከተተ፤ የተወሠኑት ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ያስገቡት ሠነድ ላይ የዕቅድ አወጣጥና ዘዴ ክፍተት በመታየቱ እንደሆነ ገልጸዋል።

Share this post