የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ይህንን ይመስላሉ
የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ይህንን ይመስላሉ። ፓለቲካ ፓርቲዎች እና ሲቪል ማህበራት ይህንን የማስተማሪያ ድምጽ መስጫ ወረቀት መጠቀም ትችላላችሁ።
የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ይህንን ይመስላሉ። ፓለቲካ ፓርቲዎች እና ሲቪል ማህበራት ይህንን የማስተማሪያ ድምጽ መስጫ ወረቀት መጠቀም ትችላላችሁ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር ካከናወነ በኋላ ባደረገው ስብሰባ ከ6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ ጋር የተያያዙ ውሳኔ የሚያስፈልጋቸው ጉዳዮች ላይ የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፏል።
1. 6ተኛው አጠቃላይ ምርጫ በተያዘለት የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም የሚካሄድ ሲሆን አስቀድሞ እንደተገለጸው በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ በእለቱ ድምጽ መስጠት የማይቻልባቸው አካባቢዎች ድምጽ አሰጣጥ ጷግሜ 01 ቀን 2013 ዓ.ም ይከናወናል።
እነዚህም
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ዛሬ ሰኔ 02 ቀን 2013 ዓ.ም የምክክር መድረክ አከናውኗል። ይህ በተደጋጋሚ ከሚደረጉ የምክክር መድረኮች አንዱ የሆነው ከፓርቲዎች ጋር የሚደረገው ምክክር በዋናነት ቦርዱ የድምጽ መስጫ ወረቀት ህትመትን አስመልክቶ ያጋጠመውን ተግዳሮት ለፓርቲዎች ሪፓርት ያቀረበበት ነው።
የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ በሪፓርታቸው እንዳቀረቡት የእጩዎችን ቁጥር መሰረት አድርጎ በተደረገው የገንዘብ ድጋፍ ወቅት ፓርቲዎች የእጩዎች ቁጥር ላይ ባቀረቡት አቤቱታ፣ በማስከተልም በድምጽ መስጫ ወረቀት እና በውጤት ማሳወቂያ ፎርሞች መካከል የማስታረቅ ስራ ሲሰራ የተወሰኑ የምርጫ ክልሎች የድምጽ መስጫ ወረቀቶች ላይ የተለያዩ ጉድለቶች መገኘታቸውን አሳውቀዋል። በዚህም መሰረት የቦርዱ ኦፕሬሽን ክፍል ባከናወነው ኦዲት 54 የምርጫ ክልሎች ድምጽ መስጫ ወረቀቶች ድጋሚ ህትመት የሚያስፈልጋቸው ሆነው ተገኝተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በክስ ሂደት ላያ ያሉ የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የምርጫ ክልሎች
እንዲሁም የተወካዮች ምክር ቤት
ምርጫ ክልል 26 እና 27 በእጩነት ለመወዳደር ጥያቄ አቅርበው እንዳልተቀበለው ይታወቃል።
በዚህም መሰረት መጀመሪያ የምርጫ ክልሎቹ ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴ፣ በማስከተል በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ቀጥሎ ከፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የእጩነት ምዝገባ ጥያቄው አግባብ አይደለም ብሎ ሲከራከር እንደነበር ይታወሳል። በዚህም መሰረት ከፍተኛው ፍርድ ቤትም የቦርዱን አሰራር አጽድቆ ነበር።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመራጮች ትምህርት ላይ ከተሠማሩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ተቋማት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ። ውይይቱን የቦርዱ አመራር አበራ ደገፋ (ዶ/ር) በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የመራጮች ትምህርት ለሚያስተምሩ 167 የሲቪክ ማኅበራት ፍቃድ የሰጠ መሆኑን ገልጸው፤ እነዚህም ፈቃድ የተሰጣቸው የሲቪክ ማኅበራት በሰጡት የመራጮች ትምህርት አማካኝነት ካርድ የወሰዱ ዜጎች ቁጥር መሻሻል ያሳየ መሆኑ፤ ለዚህም ከፍተኛ አክብሮት እንዳላቸው ተናግረዋል። ሲቪክ ማኅበራቱ በቀጣይ በሚከናወነው የድምፅ አሰጣጥ ሂደት ዜጎች በንቃት እንዲሣተፉና ድምፃቸውን በነፃነት ለፈለጉት ዕጩ እንዲሰጡ ማሰተማር አሰፈላጊ መሆኑን፤ በድምፅ አሰጣጥ ሂደት በመራጮች መሳሳት የሚባክን ድምፅ እንዳይኖር በመራጮች ትምህርት አሰጣጥ ላይ የተሰማሩ የሲቪክ ማህበራት ትምሀርቱን በደንብ መስጠት እንደሚኖርባቸው፤ እንዲሁም በድኅረ ምርጫ ሁኔታዎች ሰላማዊ እንዲሆን ዜጎች የበኩላቸውን ሚና እንዲወጡ ተገቢው ትምህርትና ግንዛ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. መሆኑን ተከትሎ ከመገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ጋር በመተባበር ተጨማሪ የቅስቀሳ የአየር ሰአት ድልድል ዛሬ አከናውነዋል። በዚህም መሰረት የፓለቲካ ፓርቲዎች የምረጡኝ ዘመቻቸውን እስከ ሰኔ 09 ቀን 2013 ዓ.ም. ድረስ ማከናወን የሚችሉ ሲሆን ከሰኔ 10-13 ድረስ ምንም አይነት ቅስቀሳ የማይደረግበት የፀጥታ ጊዜ ይሆናል። የመገናኛ ብዙሃን የአየር ሰአት ድልድሉም እስከ ሰኔ 09 ድረስ የሚቆይ ነው። ፓለቲካ ፓርቲዎች ተጨማሪውን የአየር ሰአት ድልድል ሰነድ ከቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎች የስራ ክፍል በግንባር በመምጣት መውሰድ ወይም media [at] nebe.org .et ኢሜይል አድራሻ ላይ ጥያቄ በማቅረብ በሶፍት ኮፒ ማግኘት ይችላሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከመንግስት ግብዣ መሰረት 6ተኛው አገር አቀፍ ምርጫ በጋራ ለመታዘብ በጋራ ለሚሰሩት ለአለም አቀፍ ሪፕብሊካን ኢንስቲቲዩት (IRI) ለአለም አቀፍ ዴሞክራቲክ ኢንስቲቲዮት (NDI) የምርጫ መታዘብ እውቅናን ሰጥቷል። ቦርዱ የድርጅቶቹ የጋራ የታዛቢ ቡድን ያቀረበውን የጥናት ዘዴ በማየት እንዲሁም በአለም አቀፍ ታዛቢዎች መሰረታዊ መርህዎችን እና የታዛቢዎች አለም አቀፍ የስነምግባር ደንብ በተከተለ መልኩ እንደሚሰሩ ስምምነት ላይ በመድረስ የመታዘብ እውቅናውን የሰጠ ሲሆን በአለም አቀፉ የኮቪድ ወረርሽኝ የተነሳ የታዛቢ ቡድኑ የሚያከናውነው የመታዘብ ተግባር የስፋት ውስንነት እንደሚኖረውና ይህንንም በሚያደርጋቸው ስራዎች እና ማጠቃለያዎች ላይ የሚገለጽ መሆኑን ታዛቢ ቡድኑ እና ቦርዱ በጋራ መግባባት ላይ ደርሰዋል።
ቦርዱ ከዚህ በፊት ለ45 የአገር ውስጥ የምርጫ ታዛቢዎች እውቅና መስጠቱ ይታወሳል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት 2ተኛ ሰበር ሰሚ ችሎት የወሰነውን ውሳኔ አስመልክቶ ዝርዝር የአፈጻጸም ማብራሪያ የጠየቀበት ጽሁፍ ከስር ከሚገኘው ሊንክ ላይ ማግኘት ይቻላል።
ደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
ባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ ለቦርዱ በእጩነት አቅርቧቸው የነበሩ የፓርቲው አባላትን አስመልክቶ የፍ/ቤት ውሳኔ እንዲፈጸም በደብዳቤ ላቀረቡት ጥያቄ ቦርዱ የሰጠው ምላሽ