Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን አስመልክቶ እያስጠና ያለው ጥናት ላይ ውይይት አካሄደ

መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ.ም. የባለድርሻ አካላትን ምክረ-ሃሳብ ለመሰብሰብ ታስቦ የተዘጋጀውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ብዙወርቅ ከተተ ሲሆኑ፤ በንግግርቸውም ጥናቱን ያከናወኑትን ባለሞያዎችንና የመድረኩ ተሣታፊዎች አመስግነው፤ ከመድረኩ የሚገኙት አስተያየቶች ጥናቱን በተሻለ ለማዳበር ወሣኝ ከመሆኑም ባሻገር ቦርዱ በቀጣይ ለሚያካሂዳቸው ምርጫዎች ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ገልጸዋል። አክለውም ጥናቱ በምርጫ ቦርድ ታሪክ ምናልባትም በዓይነቱ የመጀመሪያ ሊባል የሚችል ነው ብለዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ. ም. አካሂደዋለሁ ያለውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ የሰጠዉ ምላሽ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ. ም. አካሂደዋለሁ ያለውን ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ያስገባውን ሠነድ መርምሮ ሕጉንና የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ የተከተለ ሆኖ ስላላገኘው ውድቅ አድርጎታል።

የውሣኔውን ሙሉ ዝርዝር እዚህ ላይ ያገኙታል

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ (ኢዜማ). ሰኔ 25 እና 26 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በተመለከተ በቀረቡለት አቤቱታዎች ላይ ተከታዮቹን ውሣኔዎች አስተላልፏል

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ አባል የሆኑት እነአቶ ዘመኑ ሞላ (ስድስት ሰዎች) ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም. ጽፈው ባቀረቡት አቤቱታ ፓርቲው ሰኔ 25 እና 26 ቀን 2014 ዓ.ም. ባከናወነው 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ የተለያዩ የደንብ ጥሠቶች ተፈጽመዋል በማለት ለቦርዱ ሰኔ 21 እና 29 እንዲሁም ሐምሌ 5 ቀን 2014 ዓ.ም. ያቀረቡትን አቤቱታ ለማጠናከር ይረዳል ያሉትን ተጨማሪ ማስረጃዎችን አቅርበዋል። በሌላ በኩል እነአቶ ደሳለኝ በዛብህ (ሁለት ሰዎች) እንዲሁ ሰኔ 29 ቀን 2014 ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ ተመሳሳይ አየቱታ አቅርበዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚያካሄደው ሕዝበ ውሳኔ የ541 ሚሊዮን ብር የበጀት ጥያቄ አቀረበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ውስጥ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ ማስፈጸሚያ የሚያስፈልገውን የአምስት መቶ አርባ አንድ ሚልዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺህ አንድ መቶ አራት ብር ከሰማንያ ሁለት ሳንቲም (የ541,270,104.82) በጀት ያቀረበው ለኢፌዴሪ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ነው።

ቦርዱ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር የሚገኙ ስድስት ዞኖች ማለትም የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም አምስት ልዩ ወረዳዎችን እነዚሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ልዩ ወረዳዎች ላይ ሕዝበ ውሳኔ እንደሚያካሄድ ይታወቃል።

Share this post

የብልፅግና ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤን አስመልክቶ በቦርዱ የተሰጠው ውሳኔ ማጠቃለያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ብልጽግና ፓርቲ ከመጋቢት 2 እስከ 4 ቀን 2014 ዓ.ም. ድረስ ያደረገውን 1ኛ ጠቅላላ ጉባዔ አስመልክቶ ውሳኔዎችን በማሳለፍ ለፓርቲው አሳውቋል።

በዚህም መሠረት የውሳኔው አንኳር ነጥቦች የሚከተሉት ናቸው፦

በፓርቲው በጉባዔው የተመረጡ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ዝርዝር የቦርዱ ታዛቢዎች በወቅቱ የምርጫው ውጤት ሲገለፅ መዝግበው ካቀረቡት ዝርዝር ጋር ልዩነት መኖሩን አረጋግጦ የማእከላዊ ኮሚቴ አባላቱ ቦርዱ ምርጫውን ሲታዘቡ መዝግቦ የያዛቸው መሆናቸውን በመጨረሻ የወሰነ ሲሆን ስም ዝርዝራቸውንም ከውሳኔው ጋር አያይዞ ልኳል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት ያካሄደው ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ነው፡፡ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳን ጨምሮ የቦርድ አመራር አባላትና የጽ/ቤት ኃላፊ በተገኙበት ውይይት፤ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ ተሳትፈዋል፡፡

Share this post

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 ዓ.ም. እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዓ.ም. መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡

በዚህም መሠረት በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 66 ንዑስ አንቀጽ አንድ ላይ ማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ በኢትዮጵያ ውስጥ በፖለቲካ ፓርቲነት ለመንቀሳቀስ የሚችለው በሕጉ መሠረት በቦርዱ ተመዝግቦ የሕጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሲያገኝ ብቻ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለክልል ቅ/ጽ/ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች የሕግ ማዕቀፍ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕግ ማዕቀፍ ላይ በማተኮር ለቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሥልጠና የሰጠው ነሐሴ 10 እና 11 ቀን 2014 ዓ.ም ነው።

ሥልጠናው በቦርዱ አመራር አባል የሆኑት ፍቅሬ ገ/ሕይወት ንግግር ተከፍቷል። አመራሩ በንግግራቸው የቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት ኃላፊዎችና ሠራተኞች እንዲሁም የምርጫ አስፈጻሚዎች በ6ተኛው ሀገራዊ ምርጫ የነበራቸውን አስተዋፅዖ በማንሳት ምሥጋና አቅርበዋል።

አያይዘውም ቦርዱ እንደ አዲስ የተቋቋመ በመሆኑ በጊዜው በርካታ እቅዶች ቢኖሩም ከጊዜና ከሁኔታዎች አንጻር የታቀደውን ሁሉ በሚፈለገው መጠን መፈፀም እንዳልተቻለ የጠቆሙ ሲሆን፣ አሁን ግን እነዚህን ጉዳዮች ለመተግበር አመቺ ሁኔታ ስለተፈጠረ በተለይ በቀጣይ ለሚደረገው ትልቅ ዐቅም ለሚጠይቀው የአካባቢ ምርጫ ይህ ሥልጠና የሚኖረውን አስተዋፅዖ አብራርተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን የተመለከተ ያስጠናው ጥናት ላይ ባለድርሻ አካላትን አወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነሐሴ 9 ቀን 2014 ዓ.ም. የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን የተመለከተ ያስጠናው ጥናት ላይ ባለድርሻ አካላትን አወያየ። የውይይቱ ዋና ዐላማ በኢትዮጵያ ለ5ኛው ጊዜ የሚካሄደውን የአካባቢ ምርጫ ለማከናወን በሚደረገው ዝግጅት ላይ የአካባቢ ምርጫን አጠቃላይ ባህሪና አሠራር አስመልክቶ ምርጫ ቦርዱ ባስጠናው ጥናት ላይ ጥናቱ የተከናወነባቸውን ሳይንሳዊ ዘዴዎች፣ በጥናቱ የተገኙ ልምዶችን ፣ ተግዳሮቶችን፣ እንዲሁም ምክረ ሃሳቦችን ጥናቱን ባካሄዱት በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ የፈደራሊዝም እና አስተዳድር ጥናት/ ትምህርት ክፍል (Centre for Federalism and Governance Studies Addis Ababa University) በሚሠሩ ከፍተኛ የዘርፉ ተመራማሪዎች በማቅረብ አፈጻጸሙን አስመልክቶ ባለድርሻ አካላትን በማወያየት ሃሳብ ለመሰብሰብ ያለመ ነው።

Share this post