የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ፆታን መሠረት ያደረጉ ጥቃቶችን አስመልክቶ እያስጠና ያለው ጥናት ላይ ውይይት አካሄደ
መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ.ም. የባለድርሻ አካላትን ምክረ-ሃሳብ ለመሰብሰብ ታስቦ የተዘጋጀውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ብዙወርቅ ከተተ ሲሆኑ፤ በንግግርቸውም ጥናቱን ያከናወኑትን ባለሞያዎችንና የመድረኩ ተሣታፊዎች አመስግነው፤ ከመድረኩ የሚገኙት አስተያየቶች ጥናቱን በተሻለ ለማዳበር ወሣኝ ከመሆኑም ባሻገር ቦርዱ በቀጣይ ለሚያካሂዳቸው ምርጫዎች ትልቅ አስተዋፅዖ እንደሚኖረው ገልጸዋል። አክለውም ጥናቱ በምርጫ ቦርድ ታሪክ ምናልባትም በዓይነቱ የመጀመሪያ ሊባል የሚችል ነው ብለዋል።