Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ባደረገዉ ማሻሻያ ላይ ቦረዱ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ጠቅላላ ጉባኤ ማካሄዱን ተከትሎ የፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ ላይ ማሻሻያ ማድረጉን ለቦርዱ ሪፓርት አቅርቧል፡፡ ቦርዱም ፓርቲው ያወጣውን ማሻሻያ ደንብ በመመርመር ያልተሟሉ ጉዳዮች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ውሳኔውን ያሳወቀበት ደብዳቤ ከስር ያገኙታል፡፡

  PDFእዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የሰጠዉ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦሮሞ ነፃነት ንቅናቄ ፓርቲ (ኦነን) ጠቅላላ ጉባኤውን አስመልክቶ የቀረቡ አጠራጣሪ ሰነዶችን አስመልክቶ ምርመራ እንዲደረግ ለፌደራል ፓሊስ ጥያቄ ያቀረበ ሲሆን ምርመራው ተጣርቶ እስኪጠናቀቅ ፓርቲው በአዋጅ 1162/2011 አንቀፅ 98/3 መሰረት መታገዱን ይገልፃል።

 PDFደብዳቤዉን ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ባካሄደው ምክክር ወቅት ይፋ ያደረገው ለፓርቲዎች የሚሰጥ የገንዘብ ድጋፍ መጠን ከስር ይገኛል። የገንዘብ ድጋፉ ከዚህ ቀደም በፀደቀው መመሪያ ላይ በተቀመጡ መስፈርቶች መሰረት የተከናወነ ነው።

 PDFየገንዘብ ድጋፍ መጠን ለማግኘት አዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኦነግ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት አስመልክቶ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኦነግ አመራሮች መካከል የተፈጠረውን አለመግባባት አስመልክቶ የቀረቡለትን አቤቱታዎች በማየት ውሳኔ መስጠቱ ይታወሳል። በውሳኔው ቅር የተሰኙት የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር እነ አራርሶ ቢቂላ ጉዳዮን ወደፍርድ ቤት በመውሰዳቸው ክርክር ሲደረግበት ቆይቶ የሰበር ሰሚ ችሎት የሁለቱንም ወገኖች የመሰማት መብት በመጠበቅ አስተዳደራዊ ውሳኔ እንዲሰጥበት ወደቦርዱ መልሶታል። በዚህም መሰረት ቦርዱ የተለያዩ ምርመራዎችን በማድረግ የፍርድ ቤቱን ትእዛዝ ተከትሎ ያሳለፈው ውሳኔ የሚከተለው ሲሆን ለሁለቱም ተከራካሪ ቡድኖች እንዲደርስ ተደርጓል።

Share this post

የስራ ቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ዋና መስሪያ ቤት እና ለክልል ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቶች በተለያዩ የስራ መደቦች ተፈላጊውን የስራ ችሎታ እና ልምድ የሚያሟሉ ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ ፍላጎት ያላችሁ እና መስፈርቱን የምታሟሉ ሁሉ ከታች የሚገኘውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም እንድታመለክቱ እናበረታታለን፡፡

አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣ በ10 ቀናት ውስጥ በኢሜል አድራሻችን hr.dept [at] nebe.org.et ብቻ ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

Share this post

ማብራሪያ ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 26 የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያደርጉ ባስታወቀው መሰረት የፓርቲዎች የጠቅላላ ጉባኤ ሲያካሂዱና ለማካሄድም ዝግጅት ሲያደርጉ ቆይተዋል። በዚህም መሰረት የፓርቲዎች የጠቅላላ ጉባኤ ሁኔታ ማጠቃለያ የሚከተለውን ይመስላል።

ጠቅላላ ጉባኤ ያካሄዱ ፓርቲዎች

  1. ብልጽግና ፓርቲ
  2. ህዳሴ ፓርቲ
  3. ካፋ አረንጓዴ ፓርቲ
  4. የጋምቤላ ህዝብ ነጻነት ንቅናቄ

ጠቅላላ ጉባኤ ለማካሄድ በጊዜ ገደቡ መሰረት ቀን ያሳወቁ ፓርቲዎች

Share this post

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ህዳር 23 ቀን 2014 ከፓርቲዎች ጋር ባደረገው ምክክር በአዋጅ ቁጥር 1162/11 እና በመመሪያ ቁጥር 3/2011 መሠረት ከ6ተኛው አገራዊ ምርጫ መጠናቀቅ በኋላ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲያካሂዱና የሰነድ ማሻሻያ እንዲያደርጉ የተገለፀላቸው ፓርቲዎች የሚጠበቅባቸውን አጠናቀው ባለማቅረባቸው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ በተነሳ በአንድ ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤያቸውን እንዲያከናውኑ እና ለቦርዱ እንዲያስገቡ መወሰኑ በምክክሩ ወቅትም ለፓርቲዎች መገለጹ ይታወሳል።

በዚህም መሰረት የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በትላንትናው እለት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ ከስር ስማችሁ የተዘረዘረ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ በማከናወን እንዲሁም አስፈላጊ የሰነድ ማሻሻያዎችን በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ በማድረግ እንድታስገቡ እናሳስባለን።

አገራዊ ፓርቲዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 25 ቀን 2014 ዓ.ም ከፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አካሄደ። ምክክሩን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳና የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ የመሩት ሲሆን፤ በምክክሩም የፖለቲካ ፓርቲዎች የአስቸኳይ ጊዜ ዐዋጁን ተከትሎ በአባላቶቻቸውና በአመራሮቻቸው አግባብ ያልሆነ እሥር እና እንግልት እንደተፈፀመ በመግለፅ ባቀረቡት አቤቱታ መሠረት የቦርዱ ተወካይ ሰብሳቢ፣ የአቤቱታ አቅራቢ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች እና የብልጽግና ፓርቲ ተወካይ አባል የተካተቱበት አጣሪ ቡድኖች ተቋቁመው የቀረቡ አቤቱታዎችን ለማጣራት አቤቱታ ወደቀረበባቸው ክልሎች በመንቀሳቀስ እንዲያጣሩ መደረጉን ተከትሎ የተገኙ ውጤቶችን ተመልክተዋል።

Share this post

የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባን አስመልክቶ ቦርዱ የሰጣቸው አዳዲስ ውሳኔዎች አጭር መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዋጅ 1162/2011 አንቀጽ 65 መሰረት የፓለቲካ ፓርቲዎችን ምዝገባ እና ድጋሚ ምዝገባ ሲያከናውን እንደነበር ይታወቃል። በዚህም መሰረት ምዝገባቸው የታደሰላቸው ፓርቲዎች እንዳሉ ሁሉ ምዝገባ መስፈርቱን ያላሟሉ ከ27 በላይ ፓርቲዎችን መሰረዙ ይታወሳል። በህጉ መሰረትም በቦርዱ ውሳኔ ቅር የተሰኙ የተለያዩ ፓርቲዎች ወደፍርድ ቤት በመሄድ ክርክር ሲያደርጉ ቆይተዋል።

ከነዚህ ፓለቲካ ድርጅቶች መካከል

1. ኦሮሞ ኦቦ ነጻነት ግንባር ( ኦአነግ)

2. የኦሮሞ አንድነትና ዴሞክራሲ የፌዴራል የሰላም ለውጥ ( ኦአዴፌሰለ)

3. የኦሮሞ ነጻነት አንድነት ግንባር ( ኦነአግ)

4. ኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ህብረት ( ኦዳ)