Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቦርዱ ያወጣቸውን መመሪያዎች አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ለሁለት የተለያዩ ቀናት ያደረገውን ምክክር አጠናቀቀ

ሕዳር 03 እና 04 ቀን 2013 አም በተከናወኑት ምክክሮች ውይይት የተደረገባቸው መመሪዎች

- የእጩ ተወዳዳሪዎች ምዝገባ አፈፃፀም መመሪያ
-የድጋፍ ፊርማ አሰባሰብ እና መለያ ምልክት አመራረጥ መመሪያ
-የምርጫ ውድድር ቅስቀሳ ስነ ምግባር መመሪያ
-የአለምአቀፍ የምርጫ ታዛቢዎች ፍቃድ አሰጣጥ፣ የአሠራር ሥርዓት እና የሥነ ምግባር መመሪያዎች ሲሆኑ ፓለቲካ ፓርቲዎች ከህግ፣ ከልምድ እና ከቀድሞ አሰራሮች በመነሳት የተለያዩ ግብአቶችን ሰጥተዋል፡፡

ምክክሩ ቦርዱ የፓለቲካ ፓርቲዎችን ግብአት ለማካተት ከሚያደርጋቸው ተከታታይ ምክክሮች መካከል አንዱ ሲሆን በተከታዩ ሳምንትም በሌሎች መመሪያዎች ላይ በሚደረግ ውይይት የሚቀጥል ይሆናል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለተከታታይ ቀናት ሲያደርገው የነበረው ምክክር ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለተከታታይ ሶስት ቀናት ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርግ የነበረውን ውይይት ጥቅምት 23 ቀን 2013 ዓ.ም አጠናቋል፡፡ በውይይቱ የሲቪል ማህበራት ድርጅቶች፣ የሚዲያ ማህበረሰብ አባላት እና የፓለቲካ ፓርቲዎች ተገኝተዋል፡፡ በምክክር መድረኩ የተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች የኮቪድ ወረርሽኝ ውስጥ በሚደረግ ምርጫ ዋና ዋና ዝግጅቶች ምን ይመስላሉ? ከባለድርሻ አካላት ምን ይጠበቃል? የቦርዱስ ዝግጅት ምን ይመስላል? ዋና ዋና የምርጫ ተግባራት መቼ ይደረጋሉ? የምርጫ የጸጥታ ችግሮችስ እንዴት መታየት አለባቸው የሚሉ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተደርጓል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስለመጪው አገራዊ ምርጫ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመጪው አገራዊ ምርጫ የሚያስፈልጉ ዝግጅቶችን አስመልክቶ ባሳለፍነው ሳምንት ከመንግስት ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡ በውይይቱ ወቅት የሚመለከታቸው ሴክተር መስሪያ ቤቶች ሚኒስትሮች የተገኙ ሲሆን ከእያንዳንዱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት የሚጠበቁ ዋና ዋና ትብብሮች ምን መሆን እንዳለባቸው ውይይት እና ስምምነት ላይ ተደርሷል፡፡ በውይይቱ ላይ የተሳተፉ ተቋማት የኢፌዴሪ የገንዘብ ሚኒስቴር፣ የጤና ሚኒስቴር፣ ሰላም ሚኒስቴር፣ መከላከያ ሚኒስቴር፣ ሳይንስ እና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርን እና የማእከላዊ ስታቲስቲክስ ባለስልጣን ሲሆኑ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ውይይቱን አስተባብሯል፡፡ በውይይቱ መሰረትም

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ የገንዘብ ሚኒስቴር - በኮቪድ ወረርሽኝ ውስጥ የሚከናወን ምርጫ በመሆኑ የሚያስፈልገውን ተጨማሪ በጀት በወቅቱ መልቀቅ፤ እና ለምርጫ አስፈጻሚዎች የግል መከላከለያ ቁሳቁሶች (PPE) ግዥ እና አቅርቦትን አስመልክቶ ልዩ እገዛ ማድረግ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ኦፕሬሽን ዝግጅቱን እና የፓርቲዎች ማእከልን ለፓለቲካ ፓርቲ አመራር አባላት አስጎበኘ

የፖለቲካ ፓርቲዎች እና የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራር አባላት ዛሬ ጥቅምት 13 ቀን 2013 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባዘጋጀው ጉብኝት ላይ የተገኙ ሲሆን በምስረታ ላይ ያለው የሴት ፓለቲካ ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት አባላትም ተሳታፊ ነበሩ፡፡

የምርጫ ኦፕሬሽን በቀድሞ ምርጫዎች እንዴት እንደነበረ እና የመጪው ምርጫ የሚኖረውን ሂደት ለማሳያነት የተዘጋጁ ምርጫ ጣቢያዎችን እና የምርጫ ቁሳቁስ መጋዘኖችን ጎብኝተዋል፡፡

በተጨማሪም ቦርዱ ለፓርቲዎች የጋራ ምክርቤት እና ለሴት ፓለቲካ ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት ያዘጋጀውን ለተለያዩ የቢሮ ስራ እና ስብሰባዎችን ለማከናወን የሚውል የፓርቲዎች ማዕከል ቢሮ ቁልፍ ለፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የሴት ፓርቲ አባላት የጋራ ምክር ቤት አስረክቧል፡፡

Share this post

የመራጮችን ትምህርት ለማስተማር ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የእውቅና ፈቃድ መጠየቂያ ላቀረባችሁ የሲቪክ ማህበራት እና ትምህርት ተቋማት በሙሉ

 
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዶክመንቶችን ማሟላት ያለባቸውን ሲቪል ማህበራት አስመልክቶ የሚከተለውን ጥሪ በተለያዩ ሚዲያዎች ሲያስነግር ቆይቷል፡፡ በመሆኑም በሚዲያ የተደረገውን ጥሪ ያልሰማችሁ እና የመራጮች ትምህርት ለማስተማር ማመልከቻ አስገብታችሁ የነበራችሁ ሲቪል ማህበራት ማስታወቂያውን ከስር ማግኘት ትችላላችሁ፡፡ 

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባርን ( ኦነግ) አመራር አባላት የቀረበለትን አቤቱታዎች አስመልክቶ የሰጠው ውሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ፓርቲ አመራር አባላት የአመራር ለውጥ እና እገዳን አስመልክቶ የተለያዩ አቤቱታዎች ሲደርሱት እንደነበር ይታወቃል፡፡
በአንድ በኩል በእነ አቶ አራርሶ ቢቂላ ነሐሴ 1 ቀን 2012 ዓ.ም. በቁጥር 06/ABO/12 እና 7/08/12 05/03/19 በቁጥር 08/ABO/12 በተፃፉ ሁለት ደብዳቤዎች የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ በፓርቲው ሊቀመንበር በአቶ ዳውድ ኢብሳ ላይ የእግድ ውሣኔ አስተላልፏል ሲሉ ለቦርዱ በማሳወቅ ቦርዱ ውሳኔውን እንዲያጸድቅላቸው ጠይቀዋል፡፡

Share this post

ሚዲያዎች የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ዝግጅትን ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጎብኝተዋል

ሚዲያዎች የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ዝግጅትን ዛሬ መስከረም 22 ቀን 2013 ዓ.ም ጎብኝተዋል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ባዘጋጀው የሚዲያዎች ጉብኝት የምርጫ ኦፕሬሽን በቀድሞ ምርጫዎች እንዴት እንደነበረ እና አሁን የሚኖረው ሂደት ምን እንደሚመስል ገለፃ ተደርጓል።

ሁለት የማሳያ ምርጫ ጣቢያዎችን (Sample polling stations) በመገንባት ቀጣዩ ምርጫ ከቀድሞ የሚለይበት የምርጫ ሂደት በማሳያ ቀርቧል። በመጀመሪያው ማሳያ የቀድሞ ምርጫ ሂደትና ልምዶች፣ በሁለተኛው ማሳያ በቀጣዮ ምርጫ አንድ የምርጫ ጣቢያ ምን እንደሚመስል እና ዋና ዋና ለውጦቹ ለእይታ ቀርበዋል። የሚዲያ ባለሞያዎቹ በቦሌ ካርጎ መጋዘን የሚገኘውንም የቁሳቁስ እሸጋ፣ እንዲሁም በምርጫ ክልል ደረጃ አገልግሎት ላይ የሚውሉ ጄኔሬተሮችን እና ላፕቶፓችንም ጎብኝተዋል።

ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመጪው ምርጫ ዝግጅት ከድምፅ መስጫ ወረቀቶች ውጪ የቀሩ ግዢዎችን ማጠናቀቁን በተለያየ ጊዜ ማሳወቁ ይታወሳል። 

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ኦፕሬሽን እያደረገ ያለውን ዝግጅት ለሚዲያ አካላት ለማስጎብኘት የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ6ተኛው አገራዊ ምርጫ ኦፕሬሽን እያደረገ ያለውን ዝግጅት ለሚዲያ አካላት ማስጎብኘት ይፈልጋል። በመሆኑም በኢትዮጵያ ብሮድካስት ባለስልጣን የተመዘገባችሁ ሚዲያዎች በሙሉ እንድትጎበኙ ተጋብዛችኃል።

የምርጫ ቁሳቁሶቹ በከፍተኛ ጥበቃ ስር የሚገኙ በመሆናቸው አንድ ሪፓርተር እና አንድ የካሜራ ባለሞያ ሙሉ ስም እና ስልክ ቁጥር እንዲሁም የሚድያውን ስም ወደ medianebe@gmail.com የኢሜል አድራሻ እስከ ነገ እረቡ ምሽት መስከረም 20 ቀን 2013 ዓ.ም 12 ሰአት ድረስ እንድትልኩልን እንጠይቃለን። በጉብኝቱ የሚሳተፉት ስማቸው የተላለፉ ባለሞያዎች ብቻ ይሆናል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ