የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካባቢ ምርጫ የሕግ ማዕቀፍ እና አፈጻጸምን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ውይይት ያካሄደው ነሐሴ 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ነው፡፡ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳን ጨምሮ የቦርድ አመራር አባላትና የጽ/ቤት ኃላፊ በተገኙበት ውይይት፤ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካይ ተሳትፈዋል፡፡