Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥርዓተ ፆታ አካታችነትን አስመልክቶ ለቦርዱ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሞያዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ.ም. የቦርዱን ተግባራት የሥርዓተ ፆታ እና አካታችነትን ባማከለ መልኩ እንዲፈጸም የሚያስችል ሥልጠና ሰጠ። ይህ የቦርዱን የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም ባለሞያዎች ዐቅም ለመገንባት ታስበው በመሰጠት ላይ ካሉት ሥልጠናዎች መካከል አንዱ የሆነው ሥልጠና ዐላማው፤ የተሣታፊዎችን የሥርዓተ ፆታ ግንዛቤ ከማሳደግም ባለፈ በፖሊሲ ቀረጻ እንዲሁም በዕቅድ አወጣጥ እና አተገባበር ላይ ታሳቢ መደረግ ስለሚኖርባቸው የሥርዓተ ፆታና አካታችነት አሠራሮች ተለይተው እንዲታወቁ ማድረግ ሲሆን፤ በተጨማሪም የሥራ ክፍሎቹን የዕለት ተለት ሥራዎቻቸውን እንዴት ሥርዓተ ፆታና አካታችነትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መፈጸም እንዳለባቸው ክኅሎት ማስጨበጥ ነው።

Share this post

በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖሊቲካ ፓርቲዎች እና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና ቦርዱን ባቋቋመው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ ምርጫውን ለመዘገብ ለሚፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን ፈቃድ ለመስጠት እና ለመከታተል የሚያስችለውን መመሪያ አርቅቆ፣ የመገናኛ ብዙኃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ የሥነ ምግባር እና አሠራር መመሪያ ቁጥር 02 /2013 አፅድቋል።

Share this post

ጀማሪ ባለሙያዎችን ለመቅጠር የወጣ ክፍት ሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥሩ ለሚገኙ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች ጀማሪ ባለሙያዎችን /Intern/ በኮንትራት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡

በዚሁም መሠረት

- በህግ፣ በኮምፒውተር ሳይንስ፣ በኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ፣ በኮምፒውተር ኢንጅነሪንግ፣ በሶሺዎሎጂ፣ ሶሻል ወርክ፣ በህዝብ አስተዳደር፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን፣ በሰው ኃብት አስተዳደር፣ በቢዝነስ ሊደርሺፕ፣ በማርኬቲንግ ማኔጅመንት፣ በአካውንቲንግና ፋይናንስ፣ በኢኮኖሚክስ፣ በግዢ እና ንብረት አስተዳደር፣ በጋዜጠኝነት እና ስነጽሁፍ፣ በግራፊክስ ዲዛይን፣ በፖለቲካል ሳይንስ እና አለምአቀፍ ግንኙነት እንዲሁም ተያያዥ የትምህርት ዘርፎች የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው/ያላት

- አማካይ የመመረቂያ ውጤታቸው 3.5 እና ከዛ በላይ የሆነ፤

- ጥሩ የሆነ የአማርኛ እና የእንግሊዘኛ ቋንቋን ክህሎት (መናገር፣ መጻፍ እና ማንበብ) ያለው/ያላት፤

በደ/ብ/ብ/ህዝቦች ክልል 6 ዞኖች እና 5 ልዩ ወረዳዎች ህዝበ ውሳኔ ዙሪያ የመራጮች ትምህርት መሰጠት ለሚፈልጉ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች ክልላዊ መንግስት ስር የሚገኙ 6 ዞኖች ማለትም የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና ደቡብ ኦሞ ዞኖች እና 5 ልዩ ወረዳዎች ማለትም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ ልዩ ልዩ ወረዳዎች ህዝበ ውሳኔ ያካሂዳል ፡፡

ዜጎች ህዝበ ውሳኔው ላይ ያላቸውን ትርጉም ያለው ተሳትፎ ለማረጋጋጥ ብሎም ተአማኒነትን ያተረፈ ሰላማዊ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ የመራጮች ትምህርት አስፈላጊነት እሙን ነው፡፡ ይህንን አላማ ለማሳካትም የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎ ትልቅ ስፍራ ይይዛል፡፡

Share this post

ለደ/ብ/ብ/ሕ/ክልል ለሚያካሄደው የሕዝበ ውሳኔ የምርጫ አስፈፃሚዎችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር የወጣ ክፍት ሥራ ቦታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልል በ6 ዞን እና በ5 ልዩ ወረዳዎች ላይ የሕዝበ ውሳኔ ለማካሄድ በዝግጅት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ ሕዝበ ውሳኔውን የሚያስፈጽሙ ሰራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጥር ይፈልጋል። በዚሁ መሰረት በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ውስጥ የምትኖሩ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነጻ የሆናችሁ ከዚህ በታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከጥቅምት 12-20 ቀን 2015 ዓ.ም ብቻ እንድታመለከቱ ቦርዱ ይጠይቃል።

ወደ ገፁ ለመግባት እዚህ ላይ ይጫኑ

የምልመላ መስፈርት፡

ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኅብር ኢትዮጵያ) በድጋሚ ጠቅላላ ጉባዔ እንዲያደርግ ቦርዱ ውሣኔ ሰጥቷል

ኅብር ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዉ ፓርቲ (ኅብር ኢትዮጵያ) መጋቢት 25 ቀን 2014 ዓ.ም. በሀዋሳ ከተማ አንደኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን የቦርዱ ታዛቢ በተገኙበት አካሂዷል፡፡ ቦርዱም የፓርቲውን የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ሪፖርትና የታዛቢውን ሪፖርት ከሕጉና ከመተዳደሪያ ደንቡ አንፃር መርምሯል፡፡

ፓርቲው በዚሁ ጉባኤው የማእከላዊ ምክር ቤት አባላት፤ የኦዲትና ቁጥጥር ኮሚሽን አባላት እና የፓርቲው ፕሬዚዳንት ምርጫ እጅ በማውጣት ያከናወነ መሆኑን ከፓርቲው እና ከታዛቢው ሪፖርት ቦርዱ ተገንዝቧል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ከአስተዳደር እና ጸጥታ አካላት ጋር ምክክር አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙት የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ ኮንሶና፣ ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም የቡርጂ፣ አማሮ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ እና አሌ ልዩ ወረዳዎች የሚያካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም ከአስተዳደር እና ጸጥታ አካለት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡

በምክክር መድረኩ የሕዝብ ውሣኔው አጠቃላይ ዕቅድና አፈጻጸሙን በተመለከተ ገለጻ ተደርጓል። የህዝበ ውሳኔውን ሰላማዊነት ከማረጋጋጥ እና ከሎጅስቲክስ አንፃር የክልሉ እና የአካባቢ አስተዳደር መዋቅሮች ያለባቸው ሀላፊነት በተመለከተም ማብራሪያ ተሰጥቷል።

Share this post

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና በኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት መካከል የጋራ ስምምነት ሠነድ (Memorandum of Understanding) ተፈረመ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ እና በጋራ ምክር ቤቱ ዋና ሰብሳቢ መብራቱ አለሙ (ዶ/ር) አማካኝነት ዛሬ ጥቅምት 9 ቀን 2015 ዓ.ም. የተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት ሠነድ ምክር ቤቱ መጋቢት 2011 ዓ.ም በፓርቲዎች መካከል የተፈረመውን የቃል ኪዳን ሠነድ ዐላማ ለማሳካት ለሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ቦርዱ ድጋፍ ለማድረግ ይችል ዘንድ፤ እንዲሁም ምክር ቤቱም የሚሰጠውን ድጋፍ በመግባቢያ ሠነዱ ውስጥ በተጣለበት ኃላፊነት መሠረት ለታለመለት ዐላማ ማዋሉን ለማረጋገጥ የተፈረመ ነው፡፡

በዚህ የመግባቢያ ስምምነት መሠረት ቦርዱ ለምክር ቤቱ ድጋፍ ከሚያደርግባቸውና ከምክር ቤቱ ጋር የጋራ መግባባት ከተደረሰባቸው ውስጥ : -

• የምክር ቤቱ ገጽታ ግንባታ ስራዎች (ለመጽሔት ዝግጅት፤ ለማስታወቂያና ተዛማጅ ስራዎች )

• ፕሬስ ኮንፈረንስ ማዘጋጀት፣

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 1 እና 2 ቀን 2015 ዓ.ም. በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ የጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ጌዲዮ፣ኮንሶና፣ደቡብ ኦሞ ዞኖች እንዲሁም የቡርጂ፣አማሮ፣ደራሼ፣ባስኬቶ፣አሌ ልዩ ወረዳዎች የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄዷል። የመድረኩ ዐላማ የሕዝበ ውሣኔው አጠቃላይ ዕቅድና የዝግጅት መለኪያዎች፣ የሕዝበ ውሣኔው አደረጃጀት፣ እያንዳንዱን የታቀዱ ተግባራት ለመፈጸም የሚያስፈልገው የጊዜ ሁኔታ፣ ከአስተዳደር አካላትና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት የሚጠበቁ ኃላፊነቶችን አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከርና ተጨማሪ ግብዓት በመውሰድ የመጨረሻውን የጊዜ ሠሌዳ ማዘጋጀት እንደሆነ ተጠቅሷል ፡፡

Share this post

የአጭር ጊዜ ሥራ ቅጥር ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ ከተመዘገቡት የመራጮች መዝገብ መረጃ ውስጥ በሙከራ ደረጃ ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ሥራ (pilot Voters List Digitization and Auditing) ለማሠራት ባቀደው መሠረት ሥራውን ለማከናወን የሚችሉ ብቃት ያላቸውን ባለሞያዎች መልምሎ ለአጭር ጊዜ መቅጠር ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም መረጃን ወደ መረጃ ቋት የማስገባት (Data Encoding) የሥራ ልምድ ያላቸሁ፡-

1. በማንኛውም የትምህርት ዘርፍ ቢያንስ በድግሪ የተመረቃችሁ

2. ቢያንስ የአንድ ዓመት የሥራ ልምድ (በተለይ በዳታ ማስገባት (Data encoding) ላይ ልምድ ያላቸው ቢሆን ይመረጣል)

3. የሥራ ቋንቋውን አቀላጥፈው ማንበብና መፃፍ የሚችሉ

4. ሴቶች አመልካቾች የሥራ ልምዱ ካላቸውና ሌሎች መስፈርቶችን የሚያሟሉ ከሆነ ቅድሚያ ይሰጣቸዋል።