የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥርዓተ ፆታ አካታችነትን አስመልክቶ ለቦርዱ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ባለሞያዎች ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ.ም. የቦርዱን ተግባራት የሥርዓተ ፆታ እና አካታችነትን ባማከለ መልኩ እንዲፈጸም የሚያስችል ሥልጠና ሰጠ። ይህ የቦርዱን የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እንዲሁም ባለሞያዎች ዐቅም ለመገንባት ታስበው በመሰጠት ላይ ካሉት ሥልጠናዎች መካከል አንዱ የሆነው ሥልጠና ዐላማው፤ የተሣታፊዎችን የሥርዓተ ፆታ ግንዛቤ ከማሳደግም ባለፈ በፖሊሲ ቀረጻ እንዲሁም በዕቅድ አወጣጥ እና አተገባበር ላይ ታሳቢ መደረግ ስለሚኖርባቸው የሥርዓተ ፆታና አካታችነት አሠራሮች ተለይተው እንዲታወቁ ማድረግ ሲሆን፤ በተጨማሪም የሥራ ክፍሎቹን የዕለት ተለት ሥራዎቻቸውን እንዴት ሥርዓተ ፆታና አካታችነትን ታሳቢ ባደረገ መልኩ መፈጸም እንዳለባቸው ክኅሎት ማስጨበጥ ነው።