የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከባለድርሻ አካላት ጋር በሁለት ረቂቅ መመሪያዎች ላይ ውይይት አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ውይይት ያደረገባቸው ሁለት ረቂቅ መመሪያዎቹ፤ በምርጫ ወቅት የኮቪድ 19 ሥርጭትን ለመቀነስና በምርጫ ሂደት ላይ ሰላምና ፀጥታን የሚያስከብሩ የፀጥታ አስከባሪ አካላት የአሠራር ሥርዓት እና የሥነ-ምግባር ድንጋጌዎችን የያዙ ናቸው። የመጀመሪያው የውይይት መድረክ ባሳለፍነው ሳምንት ጥር 14 ቀን 2013 ዓ.ም ከጤና ባለሞያዎች፣ ከፓለቲካ ፓርቲዎችና ከፀጥታ አካላት ጋር የተደረገ ሲሆን፤ ቀጣዩና በዛሬው ዕለት ጥር 18 ቀን 2013 ዓ.ም የተደረገው ውይይት ደግሞ ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና ከባለድርሻ አካላት ጋር ተደርጎ ውሏል።