Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ ያለውን የቁሳቁስ ዝግጅት አስጎበኘ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ለመራጮች ምዝገባ ያለውን የቁሳቁስ ዝግጅት ለብዙኃን መገናኛ አካላት አስጎበኘ። በቦሌ ዐየር ማረፊያ ካርጎ በሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ መጋዘን በመከናወን ላይ ያለውን አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሥራ ምን እንደሚመስል ማስተዋወቅ ዐላማው ያደረገው ጉብኝት፤ በቦርዱ የኮሚኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ገለጻ የተጀመረ ሲሆን፤ ኃላፊዋ ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ያለውን አጠቃላይ ዝግጁነት የሎጂስቲክና የሎጂስቲክ ሥርጭት ዕቅድ አወጣጡን ጨምረው አብራርተዋል።

Share this post

አጭር መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በአቶ አራርሶ ቢቂላ በተጻፈ ደብዳቤ ሁለተኛውን ጠቅላላ ጉባዔ መጋቢት 4 ቀን 2013 ዓ.ም. አካሂዶ መተዳደሪያ ደንቡን ማሻሻሉን፣ የፓርቲውንም ብሔራዊ ምክር ቤት መምረጡን እንዲሁም በማግስቱ መጋቢት 5 ቀን 2013 ዓ.ም. የድርጅቱን ብሔራዊ ምክር ቤት ተሰብስቦ የፓርቲውን ከፍተኛ አመራሮች መምረጡን ያስረዳሉ የተባሉ ሠነዶች በዛሬው እለት መጋቢት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስገባ ሲሆን ቦርዱ ለወደፊት እነዚህን ሰነዶች የሚመረምር እና አስፈላጊውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን ይገልጻል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ ስልጠናዎችን አከናወነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም የካቲት 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ.ም ለመራጮች ምዝገባ የአሠልጣኞች ሥልጠና መስጠቱ ይታወሳል። የአሠልጣኞች ሥልጠናው ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለዞን አስተባባሪዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና ለልዮ ምርጫ ጣቢያ ሠራተኞች እንዲሁም ለመሥክ አሠልጣኞች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የነበረ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞቹ ደግሞ መጋቢት 4 እና 5 ቀን 2013 ዓ.ም ሥልጠናው ተሰጥቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛዉን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ለሲቪል ማህበራት እውቅና የመስጠት ስራውን አጠናቀቀ። 134,109 የአገር ውስጥ ታዛቢዎች ይሰማራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ስራውን አጠናቀቀ። 134,109 የአገር ውስጥ ታዛቢዎች ይሰማራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫን ለመታዘብ ፍላጎት ላላቸው የሀገር ዉስጥ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ፍቃድ ለማግኘት ማመልከቻዎቻቸውን እንዲያቀርቡ ባወጣዉ ማስታወቂያ መሰረት 111 ድርጅቶች እውቅናን ለማግኘት ያመለከቱ ሲሆን ድርጅቶቹ ያቀረቡትን ማመልከቻዎች እና ተያያዥ ሰነዶች በምርጫ ህጉ፣ በወጣዉ ጥሪ እና በመመሪያዉ የተደነገጉትን መስፈርቶች እና ግዴታዎች ያሟሉ ስለመሆኑ፣ እንዲሁም የድርጅቶቹ የማስፈፀም አቅም ተገምግሞ፣ እና በየደረጃዉ የተጓደሉ ሰነዶችን እንዲያሟሉ በማድረግ በመጀመሪያዉ ዙር ካመለከቱ ከ111 ድርጅቶች መካከል 43ቱ ድርጅቶች ወደ ሁለተኛዉ ዙር እንዲያልፉ ተደርጓል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዕጩዎች የምዝገባ ሂደትንና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን የተመለከተ የምክክር መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 8 ቀን 2013 ዓ.ም. የዕጩዎች የምዝገባና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን የተመለከተ የምክክር መድረክ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር የብዙኃን መገናኛ አካላት በተገኙበት አካሄደ። ይህን የምርጫው የጊዜ ሠሌዳ ከወጣበት ጊዜ አንሥቶ በተከታታይና በልዩ ሁኔታ እየተደረጉ ያሉ የምክክር መድረኮች አካል የሆነውን መርኃ-ግብር በንግግር ያስጀመሩት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ሲሆኑ፤ የዕጩዎች ምዝገባና ተያያዥ የኦፕሬሽን ሥራዎችን የተመለከቱ አጠቃላይ ገለጻ ሰጥተዋል። ግልጽነትና ፍትሐዊነትን ለመጨመር ያስችል ዘንድ በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖረውን የዕጩዎች ቅደም ተከተል በሎተሪ ዕጣ እንደሚወሠንም አክለው ገልጸዋል። የሰብሳቢዋን ማብራሪያ ተከትሎ የቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባ በዕጩዎች ምዝገባ ወቅት የቀረቡ አቤቱታዎችንና መልስ የተሰጠበትን አግባብ አብራርተው የተሣታፊዎች ሃሳብ አሰተያየት እንዲሰጡበት ተደርጓል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴቶችን ያማከለ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ እና የባለድርሻ አካላት ሚናን አስመልክቶ የምክክር መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 6 ቀን 2013 ዓ.ም. ሴቶችን ያማከለ የምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ እና የባድርሻ አካላት ሚናን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎችና ከባለድርሻ አካላት ጋር የምክክር መድረክ አካሄደ። መድረኩን የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ በንግግር የከፈቱት ሲሆን፤ ሰብሳቢው በንግግራቸው ያለፉት 30 ዓመታት የሴቶችን የፖለቲካ ተሣትፎ ምን እንደሚመስል ገልጸው ያለውን መሻሻል ጥናቶችን ጠቅሰው አብራርተዋል። መሻሻል ቢኖርም እንኳን ከሚፈለገውና ሊሆን ከሚገባው አንጻር እጅግ ብዙ እንደሚቀር አክለው ገልጸዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ት/ት ፍቃድ ከተሰጣቸው ሲቪክ ማኅበራት ጋር ሁለተኛ ዙር ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ትምህርት ፍቃድ ከተሰጣቸው የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጋር ሁለተኛ ዙር የውይይት መድረክ አካሄደ። በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ የተከፈተው መድክ በተከታታይ ለሁለት ቀናት የተካሄደ ሲሆን መጋቢት 3 ቀን 2013 ዓ.ም.

Share this post