የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ በሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ፤ የመራጮች ትምህርት በመስጠት ከሚሠማሩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ምክክር እና የስልጠና መድረክ አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኅዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ከሲቪል ማኅበራቱ ጋር ያደረገውን ምክክር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ሕዝበ ውሣኔው በሚካሄድባቸው አካባቢዎች ላይ ድምፅ በመስጠት ለመሣተፍ ቅድመ ሁኔታውን የሚያሟሉ ዜጎች በነፃነትና በሰላማዊ መንገድ ፍላጎታቸውን የሚገልጹበትን ዲሞክራሲያዊ የምርጫ ዐውድ ለማረጋገጥ እንዲቻል ቦርዱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ እንደሚገኝና በዕለቱም በመራጮች ትምህርት ላይ ከተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር የሚካሄደው ምክክር የዚሁ አንድ አካል እንደሆነ ተናግረዋል። የቦርድ አመራር አባል የሆኑት አበራ ደገፉ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዜጎች በንቃት እንዲሣተፉና ፍላጎታቸውንም በነፃነት እንዲገልጹ ማሰተማር አሰፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እና ቦርዱ እንዳዲስ ከተቋቋመ በኋላ በተካሄዱት ሁለቱ ሕዝበ ውሣኔዎች ላይ የሲቪል ማኅበራቱ እና የትምህርት ተቋማት የነበራቸው ሚና የላቀ እንደ