ጥያቄ - ቦርዱ ውሳኔውን ለተወካዮች ምክር ቤት ያሳወቀው ለምንድነው?

መልስ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርዱ ተጠሪነቱ ለተወካዮች ምክር ቤት ነው፡፡ የአፈጻጸም ሪፓርቶችን የሚያቀርበውም ለምክር ቤቱ ነው በመሆኑም ውሳኔውን ለተወካዮች ምክር ቤት ከማሳወቅ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም፡፡ ቦርዱ በተሰጠው ሃላፊነት መሰረት ችግሩን ለተወካዮች ምክር ቤት ከማቅረብ እና በጥናት ላይ የተመሰረተ ውሳኔ ከማድረግ ውጨ ከስልጣኑ ውጪ የሰራው ወይም ስልጣኑ ኖሮት ሳይወጣ የቀረው ሃላፊነት የለም፡፡

ጥያቄ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰጠው መግለጫ ምርጫውን አራዝሟል? የመግለጫው ዋና ሃሳብ ምንድነው?

መልስ - የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም መግለጫ አውጥቷል፡፡ በመግለጫው ዋና አላማ ምርጫውን ቀድሞ ባቀደው ቀን ማለትም ነሐሴ 23 ቀን 2012 ዓ.ም ማከናወን እንደማይችል ማሳወቅ ሲሆን፣ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ ጥናት አካሂዷል፡፡ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተጠሪነቱ ለተወካዮች ምክር ቤት ስለሆነ ውሳኔውንም ለተወካዮች ምክር ቤት አሳውቋል፡፡ ከአቅም በላይ በሆነ ችግር ምክንያት ምርጫውን ማከናወን ካለመቻሉ በስተቀር የተራዘመ ቀን ቆርጦ አላቀረበም፡፡ ቦርዱ ማድረግ የሚችለው አለመቻሉን ብቻ ገልጾ ሪፓርት ለሚያደርግለት ለተወካዮች ምክር ቤት ማሳወቅ ብቻ ነው፡፡ 
በመግለጫው ተገለጹት የቦርዱ ዋና ዋና ውሳኔዎች የሚከተሉት ናቸው፡፡ 
• በኮቪድ19 የተነሳ ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ምርጫውን ማካሄድ የማይቻለው መሆኑን በመረዳት ያወጣውን የጊዜ ሰሌዳ በመሰረዝ በሰሌዳው መሰረት መከናወን ያለባቸው ተግባራት ለጊዜው እንዲቆሙ ፤

ማስታወቂያ ለፓለቲካ ፓርቲዎች በሙሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአገራችን በገባው ኮቪድ19 ወረርሽኝን ተከትሎ የተለያዩ የአሰራር መንገዶችን በመቀየስ ስራውን ለማከናወን ጥረት እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ የአሰራር ለውጥ የተነሳ እንዲሁም ለሁሉም አካላት ደህንነት ሲባል የተለያዩ ጉዳዮች ያላቸው የፓለቲካ ፓርቲዎችን ጠርቶ ማነጋገርን፣ ውይይት ማድረግንም ሆነ አስፈላጊውን ድጋፍ መስጠትን አዳጋች አድርጎታል፡፡