Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የክልል ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሃላፊዎች ምልመላ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዋና መስሪያ ቤት ደረጃ የጀመረውን ውስጣዊ አደረጃጀት ሪፎርም በክልል ደረጃ በማስፋት በ9 ክልሎች የሚገኙት ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶቹን እንደአዲስ እያደራጀ ይገኛል፡፡ የዚህ ስራ ዋናው አካል የክልል የምርጫ ሃላፊዎችን እንደስራ አመራር ቦርዱ አባላት አመራረጥ ሁሉ የሚመለከታቸው አካላት የተሳተፉበት እንዲሆን ማድረግ ነው፡፡ በዚህም መሰረት በዘጠኙ ክልሎች እና በሁለቱ የከተማ አስተዳደሮች በእጩነት ለመወዳደር የሚፈልጉና ከስር የተጠቀሰውን መስፈርት የሚያሟሉ ግለሰቦች የአመላመል ሂደት እንዲሁም በመጨረሻ ይህን የክልል ቅርጫፍ መስሪያ ቤት ዋና ሃላፊነትን አስመልከቶ ቦርዱ የሚሰጠው የቅጥር ውሳኔ በሚዲያ በይፋ የተገለጸ እንዲሆን ማድረግ አስፈልጓል፡፡

በዚህም መሰረት በክልል የምርጫ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ኃላፊነት በዕጩነት የሚቀርቡ አመልካቾች ማሟላት የሚኖርባቸው መስፈርቶች፡-

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ዞን ሕዝበ ውሳኔን አፈጻጸም አስመልክቶ ከክልልና ዞን ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ

ጳጉሜ 2 ቀን 2011 ዓ.ም.       

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ዞን ሕዝበ ውሳኔን አፈጻጸም አስመልክቶ የተለያዩ አካላት ጋር የሚደረጉ የተለያዩ ውይይቶችን እንደሚያከናውን ባስቀመጠው የድርጊት መርሃ ግብር መሠረት ነሐሴ 30 ቀን 2019 ዓ.ም. ከደቡብ ክልል ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ምክር ቤት ተወካዮች፣ የክልሉ አመራር አባላትና ከዞኑ ተወካዮች ጋር ውይይት አካሒዷል፡፡ በውይይቱ ላይ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች አፈጉባኤ ሄለን ደበበ፣ ምክትል አፈጉባኤ መንግሥቱ ሻንካ፣ የክልል መስተዳደር ጽ/ቤት ዋና አማካሪ አኒሳ መልኮ፣ የሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ደስታ ሌዳሞ፣ ሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጥራቱ በየነ እና ሌሎች የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች ከቦርዱ አባላት ጋር ገንቢ ውይይት አድርገዋል፡፡ በውይይቱም ላይ፦

Share this post

የሚዲያዎች ዘገባ ማስተካከያ

ሐምሌ 18 ቀን 2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያለበትን ከፍተኛ የሥራ ጫና፣ የአቅም ውስነንነት እና የሪፎርም ሥራ መደራረብ የተነሳ በዚህ ዓመት መደረግ የነበረበትን የአካባቢ ምርጫ እና የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተማ ምክር ቤቶች ምርጫ ማካሄድ እንደማይችል ለኢፌዴሪ ተወካዮች ምክር ቤት በጽሁፍ የገለጸ ቢሆንም ምርጫዎቹ ከሚቀጥለው አገራዊ ምርጫዎች ጋር እንዲካሄዱ ምክረሃሳብ ያቀረበውም ሆነ ውሳኔ ያሳለፈው የተወካዮች ምክር ቤት ነው። በመሆኑም ቦርዱ የአካባቢ ምርጫም ሆነ የሁለቱ ከተማ ምክር ቤቶች ምርጫ ከአጠቃላይ ምርጫ ጋር መካሄድ አለባቸው የሚል የውሳኔ ሀሳብ አቅርቧል የሚለው የሚዲያዎች ሪፓርት ማስተካከያ እንዲደረግበት እንጠይቃለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

ባለሞያዎች ዝርዝር ውስጥ ማካተቻ ጥሪ

ይህ የስራ ማስታወቂያ አይደለም፡፡
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተላለፈ ለባለሞያዎች ዝርዝር(Professionals roster) ውስጥ ማካተቻ ጥሪ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለፉት ስድስት ወራት የተለያዩ ተቋማዊ ለውጦችን ለማካሄድ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ከነዚህም ለውጦች መካከል ዋናው ተቋሙን ከፍተኛ አቅምና ቁርጠኝነት ያለው የሰው ሃይል እንዲኖረው ጥረት ማድረግ ነው፡፡
በዚህም መሰረት የቦርዱ ጽ/ቤት በተለያዩ ሞያዎች የከፍተኛ ክህሎት ባለቤት የሆኑ ግለሰቦችን ግለታሪክ (ካሪኩለም ቪቴ) መሰብሰብና የባለሞያዎች ዝርዝር በማዘጋጀት አስፈላጊ ሆኖም ሲገኝ በበጎ ፍቃደኝነት፣ በጊዜያዊ ኮንትራት ስራ፣ እንዲሁም በቅጥር ከተቋሙ ጋር አብረው መስራት የሚችሉበትን መንገድ ለማመቻቸት ይፈልጋል::

በአዲሱ የምርጫና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ላይ የተደረገው ውይይት

ሐምሌ 24 ቀን 2011 ዓ.ም.        

በአዲሱ የምርጫና እና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ላይ የተደረገውን ውይይት አስመልክቶ የፋና ብሮድካስቲንግ ዘገባን ማየት ይችላሉ። ዘገባው የተነሱ ጥያቄዎችንና በቦርዱ ኃላፊዎችና በህግ አርቃቂ ባለሞያዎች የተሰጡትን መልሶች ያስቃኛል።

http://bit.ly/2Q2EYSq 

 

Share this post

በአዲሱ የምርጫና እና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ ላይ ሕዝባዊ ውይይት ተደረገ

ሐምሌ 18 ቀን 2011 ዓ.ም.

በጠቅላይ አቃቤ ህግ ስር በሚገኘው በህግና በፍትህ ማሻሻያ ምክር ቤት የዴሞክራሲ ተቋማት የሥራ ቡድን አዲሱ የምርጫና የፓለቲካ ፓርቲዎች አዋጅን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጋር በመተባበርና ከተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመወያየት የተረቀቀውን ህግ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ በትላንትናው ዕለት የዴሞክራሲና የፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ለሕዝብ ክፍት የሆነ ውይይት ያዘጋጀ ሲሆን የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪክ ማህበራት ተወካዮች ተሳትፈውበታል፡፡ በዚህ ውይይት የተለያዩ በህጉ ላይ የተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን ሁለት ጉዳዮች በዋናነት ሰፊ ውይይትና ክርክር ተደርጎባቸዋል፡፡ የህግ አርቃቂ ባለሞያዎቹ እና የቦርዱ ኃላፊዎችም ለጥያቄዎቹ መልስ የሰጡ ሲሆን የህጉን መነሻ መርሆዎች በዝርዝር ማብራሪያ አቅርበዋል፡፡

ሁለቱ ከፍተኛ ክርክር የተደረገባቸው ጉዳዮች;

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ከጣልያንዋ ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል

ሰኔ 13 ቀን 2011 ዓ.ም.   

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ ከጣልያንዋ ምክትል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ጋር ተገናኝተው ውይይት አድርገዋል በውይይቱም ወቅት የሚቀጥለውን ምርጫ አስመልክቶ በጣልያን መንግሥት እና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መካከል ሊኖር ስለሚችለው ትብብር ተነጋግረዋል። ሚኒስትሯ በበኩላቸው የጣልያን መንግሥት የሚቀጥለውን ምርጫ ጋር የተያያዙ ሥራዎችን ለመደገፍ ከፍተኛ ፍላጎት እንዳለው ገልጸዋል።

Share this post