መልስ - የደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያ ህዝበ ውሳኔ ከምርጫው ጋር መደረጉ የህዝበ ውሳኔውን ኦፕሬሽን በጣም ቀላል የሚያደርገው ሲሆን ከፍተኛ ወጪንም የሚቀንስ ይሆናል፡፡ ቦርዱ ለብሔራዊ ምርጫ እየተዘጋጀ ቀድሞ ህዝበ ውሳኔ ለማደራጀት በቂ ጊዜ የማይኖረው ሲሆን ከዚያም በተጨማሪ ህዝበ ውሳኔን ለብቻው ለማደራጀት የሚወጣው ከፍተኛ ወጪ እና ዝግጅት ከብሔራዊ ምርጫ ጋር በመደረጉ በግማሽ የሚቀንስ ይሆናል። ቦርዱም አስፈጻሚዎችን በሚያሰለጥንበት ወቅት ተጨማሪ የህዝበ ውሳኔ አስተዳደር ስልጠና በመስጠት፣ ተጨማሪ የህዝበ ውሳኔ ድምጽ መስጫ ወረቀት በማተም በተመሳሳይ መራጮች ምዝገባ ሂደትን በመከተል ህዝበ ውሳኔውን ለማስፈጸም ቀላል ይሆንለታል።

6