መልስ - አንድ ሰው አንድ ቦታ በመራጭነት ለመመዝገብ በምርጫ ጣቢያው ነዋሪነቱን ተረጋግጦ ሲሆን መስፈርቱን አሟልቶ ለመመዝገቡ ደግሞ የመራጭነት መታወቂያ መያዝ አለበት። በአካባቢው ነዋሪ ያልሆነ መራጭ ተመዝግቧል የሚል ጥርጣሬ ካለ የመራጮች ምዝገባ መዝገብ በየምርጫ ጣቢያው 10 ቀን ክፍት የሚሆንበት እና ቅሬታ የሚቀርብበት ስርአት አለ፣ ፓርቲዎች፣ ታዛቢዎች እና ሲቪል ማህበራት ሂደቱን መታዘብ እና ቅሬታን ማቅረብ ይችላሉ። በተጨማሪም የመራጮች ዝርዝር ወደ ዳታ ቤዝ የሚገባ በመሆኑ የተደጋጋሚ የመራጭነት ምዝገባን በቴክኖሎጂ ለመለየት የሚቻልበት አሰራርም በቦርዱ በኩል ተዘርግቷል። በመሆኑም የድምጽ መስጫ ቀኖቹ መለያየት የምርጫውን የጥራት ደረጃ የሚጨምር እንጂ የሚቀንስ አይሆንም።

4