መልስ - ድምጽ ሰጪዎች ድምጽ የሚሰጡበት የምርጫ ክልሎች የተለያዩ በመሆናቸው በድምጽ አሰጣጥ ወቅት መምታታትን ያስከትላል፤ ምርጫ አስፈጻሚዎች ውጤት ቆጥረው ወደሚመለከተው የምርጫ ክልል የሚልኩ ሲሆን በአዲስ አበባ እና ድሬደዋ ግን ለሁለት እና ለሶስት ምርጫ ክልሎች ውጤትን አከፋፍለው እንዲልኩ ይገደዳሉ ይህም በውጤቱ ድመራ ላይ መምታታት ሊያመጣ ይችላል፣ የምርጫውን አፈጻጸምም አስቸጋሪ ያደርገዋል፤ ምርጫ አስፈጻሚዎች ለተለያዩ የምርጫ ክልሎች ውጤትን በታትነው እንዲልኩ የተለየ የቆጠራ እና የውጤት ሪፓርት አደራረግ ስልጠና ማግኘት ይኖርባቸዋል ይህም ተጨማሪ የኦፕሬሽን ጫና ከመሆኑም በላይ ለዚህ የተለየ ህትመቶችን የማዘጋጀት ተጨማሪ ጫና ያስከትላል። 

2