Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

ቦርዱ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በወሰዳቸው ሦስት ቁልፍ የምርጫ ሥርዓት ማዘመኛ ማሻሻያዎችን በተመለከተ ዎርክሾፕ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን መፈጸም ተከትሎ ሁሉምን ባለድርሻ አካላት፤ መገናኛ ብዙኃኑን ጨምሮ በተናጠል የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ስኬትና ተግዳሮት ተብለው ሊጠቀሱ የሚችሉትን ጉዳዮች በዝርዝርና በጥልቀት በመወያየት፤ የውይይቱንም ግኝት (Lesson Learned) ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአንድ ላይ ባሣተፈ መልኩ በድጋሚ አስተችቶ የማሻሻያ መፍትሔዎችን መውሰድን የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባሩ አድርጎ ሲሠራ ቆይቷል።

ቦርዱ በባለድርሻ አካላት ማሻሻያ ተጠይቆባቸው የመፍትሔ ዕርምጃ ከወሰደባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ ለአፈጻጸም አስቸጋሪ የነበሩትን የዐዋጁ አንቀጾችን በመለየት ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን እና ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮዎችን ባገናዘበ መልኩ የማሻሻያ ሃሳቦችን በባለሞያ አስጠንቶ ማቅረብ፣ የዕጩዎችንና የመራጮችን መጉላላት የሚያስቀር እና መረጃንም ዘመናዊ ሥርዓትን ጠብቆ ለማደራጀት የሚያግዝ የዲጂታይዜሽን ሥራ መሥራት ይጠቀሳሉ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለበጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ የሰጠው የአሠልጣኞች ሥልጠናን የተመለከተ የልምድ ልውውጥ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገሪቱ ውስጥ ባሉ የተለያዩ ብሔራዊ ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ላሉ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ሥልጠና በመስጠት ላይ መሆኑ ይታወቃል። ይኽንንም ተከትሎ ቦርዱ ቀደም ሲል ሥልጠናውን በተሰጠባቸው በሲዳማ እና በአፋር ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በድሬደዋ ከተማ መስተዳድሮች “በሙከራ ትግበራ ማዕቀፍ” ከአራት ዩኒቨርሲቲዎች ለተውጣጡ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ርዕሰ-ጉዳይ ላይ የሰጠው የአሠልጣኞች ሥልጠና ያስገኘው ውጤትና ያጋጠሙ ተግዳሮቶች፤ እንዲሁም የትኞቹ የሥልጠና ሥልቶች ውጤት አስገኙ የሚለው ላይ የልምድ ልውውጥ አካሄደ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሰመራ ዩኒቨርሲቲ እና ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በድኅረ ምርጫ ወቅት ከሚያከናውናቸው ዋና ዋና ተግባራት ውስጥ የሥነ¬-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት መሆኑ ይጠቀሳል። በዐዋጁም ላይ ቦርዱ ይኽንን ተግባሩን በክልልና በከተማ መስተዳድር ደረጃ በሚቋቋሙ የቦርዱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች አማካኝነት እንደሚያከናውን በተገለጸው መሠረት፤ የቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ከሚገኙ የቦርዱ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር በመተባበር በየክልሉና ከተማ መስተዳድሮቹ ለሚገኙ የብሔራዊ ዩኒቨርስቲ በጎ ፈቃደኛ ወጣቶች፤ በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ዙሪያ ሥልጠና ሰጥቷል። በዚኽም አግባብ ቦርዱ ሥልጠናው ባልተሰጠባቸው ዩኒቨርስቲዎች ሥልጠናውን መስጠት ቀጥሎ፤ ለሰመራ ዩኒቨርሲቲ እና ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ ፈቃደኛ ተማሪዎች ሰጥቷል።

Share this post

የቦርዱ ውጤታማ የፕሮግራም በጀት አተገባበር እንዲጠናከር ለቦርዱ ኃላፊዎች የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተለያዩ ሥራ ክፍሎቹ አማካኝነት ቦርዱ የተቋቋመለትን ዐላማ በብቃት መፈጸም የሚያስችለውን ሙያዊ ሥልጠና በተለያዩ ዘርፎች ላይ ሲያሰጥ ቆይቷል። ከዚኽም ጋር ተያይዞ የቦርዱን ስትራቴጂክ ዕቅድ ከመንግሥት የፕሮግራም በጀት ማዕቀፍ ጋር አቀናጅቶ የሚሠራበትን ውጤታማ የአሠራር ሥርዓት ላይ በቂ ግንዛቤ እንዲኖር ለማስቻል፤ በቦርዱ ዋና መሥሪያ ቤትና በክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ ለሚሠሩ የሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሙያዎች የአራት ቀናት የዐቅም ግንባታ ሥልጠና በኢትዮጵያ ሥራ አመራር ኢንስቲትዮት ባለሞያዎች አማካኝነት ሰጠ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ለሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሠራጨ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን እንዲሁም የመራጮች መረጃን ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች ተደራሽ ለማድረግ በትኩረት እየሠራ ይገኛል። ቦርዱ ትምህርቱን ተደራሽ ከሚያደርግባቸው ዘዴዎች አንዱ የተለያዩ የኅትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት ለተለያዩ ተቋማትና ቤተ-መጽሓፍት ተደራሽ ማድረግ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተጠናቀቀው ሣምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ-መንግሥቱ ላይ በተቀመጠውና በቦርዱ ማቋቋሚያ ዐዋጀ ላይ በተደነገገው መሠረት ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሆኑ ይታወቃል፤ በዚኽም መሠረት ቦርዱ በተጠናቀቀው ሣምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ወቅትም ሁሉም የቦርድ አመራር አባላትና የጽ/ቤት ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል፣ ግምገማና የመማማር ሥራ ክፍል ከፍተኛ ባለሞያ አማካኝነት ቦርዱ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እያደረገ ያለውን ዝግጅን ጨምሮ እስካሁን የሠራቸውንና በመሥራት ላይ ያላቸውን ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ቀርቧል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምርጫና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ የኅትመት ውጤቶችን በቤንሻንጉል-ጉሙዝ እና በአማራ ክልሎች አሠራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ዙሪያ ያላቸዉን ግንዛቤ ለማሳደግ ያግዛል ያላቸዉን ዘዴዎች በመጠቀም የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። በዚህም መሠረት የቦርዱ የሥነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ቋንቋዎች የተዘጋጁ ምርጫና ተያያዥ ጉዳዮችን የተመለከቱ የኅትመት ውጤቶችን ለዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ላይ በስፋት እየሠራ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች በአካታችነት ለማዳረስ እንዲቻል በየክልሎቹና ከተማ መስተዳድሮቹ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በጎ-ፍቃደኛ የሆኑ ወጣቶችን በመመልመል የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በመስጠት ሂደት ውስጥ ተሣታፊ እንዲሆኑ ዕቅድ ይዞ ለተግባራዊነቱ በትኩረት እየሠራ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴውን የተመለከተ ዐውደ-ጥናት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ ያሠራው የቦርዱን የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ሥነ-ዘዴ የገመገመ መነሻ ጥናት መጠናቀቁን ተከትሎ ግንቦት 7 ቀን 2017 ዓ.ም. ባካሄደው ዐዋደ-ጥናት፤ የጥናቱን ሂደትና ግኝት እንዲሁም ጥናቱን ተከትሎ የተሰጠውን ምክረ-ሃሳብ በአማካሪ ድርጅቱ ባለሞያዎች አማካኝነት ዐውደ ጥናቱ ላይ ተሣታፊ ለነበሩት የቦርዱ አመራሮች፣ ለሚመለከታቸው የቦርዱ ሥራ ክፍሎችና ባለድርሻ አካላት አቅርቧል።

Share this post