ቦርዱ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በወሰዳቸው ሦስት ቁልፍ የምርጫ ሥርዓት ማዘመኛ ማሻሻያዎችን በተመለከተ ዎርክሾፕ አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን መፈጸም ተከትሎ ሁሉምን ባለድርሻ አካላት፤ መገናኛ ብዙኃኑን ጨምሮ በተናጠል የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ስኬትና ተግዳሮት ተብለው ሊጠቀሱ የሚችሉትን ጉዳዮች በዝርዝርና በጥልቀት በመወያየት፤ የውይይቱንም ግኝት (Lesson Learned) ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአንድ ላይ ባሣተፈ መልኩ በድጋሚ አስተችቶ የማሻሻያ መፍትሔዎችን መውሰድን የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባሩ አድርጎ ሲሠራ ቆይቷል።
ቦርዱ በባለድርሻ አካላት ማሻሻያ ተጠይቆባቸው የመፍትሔ ዕርምጃ ከወሰደባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ ለአፈጻጸም አስቸጋሪ የነበሩትን የዐዋጁ አንቀጾችን በመለየት ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን እና ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮዎችን ባገናዘበ መልኩ የማሻሻያ ሃሳቦችን በባለሞያ አስጠንቶ ማቅረብ፣ የዕጩዎችንና የመራጮችን መጉላላት የሚያስቀር እና መረጃንም ዘመናዊ ሥርዓትን ጠብቆ ለማደራጀት የሚያግዝ የዲጂታይዜሽን ሥራ መሥራት ይጠቀሳሉ።