ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር ለተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል ይፋ አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በግል ዕጩነት ለመወዳደር የተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችን አወያይ። አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት የተገኙበትን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ሲሆን፤ በንግግራቸውም፤ ቦርዱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በጊዜ ሠሌዳው መሠረት ለማካሄድ ልዩ ልዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ መሆንኑ አስታውሰው፤ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድልም የዚኹ አካል መሆኑን ተናግረዋል። የውይይቱ አንዱ አጀንዳ የሆነው የነፃ የዓየር ሰዓት ድልድልን አስመልክቶ ሲናገሩም የግል ዕጩዎቹ በሚያደርጉት የምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ሕጉን ተከትለው በኃላፊነት ስሜት መሆን እንዳለበትና ይኽም የምርጫውን ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒነት በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል።