ለ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በምስል ከተለያዩ የምርጫ ክልሎች እና የምርጫ ጣቢያዎች
ለ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በምስል ከተለያዩ የምርጫ ክልሎች እና የምርጫ ጣቢያዎች
መግቢያ፣
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡
ለ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት በምስል ከተለያዩ የምርጫ ክልሎች እና የምርጫ ጣቢያዎች
ለ7ኛዉ ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ትምህርት መስጠት ሂደት ከተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች በፎቶ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የተቋቋሙ ልዩ ምርጫ ጣቢያዎች ላይ መራጮች ስለሚመርጡበት አግባብ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ.ም. ተወያየ። የውይይቱን የመክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ `ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ አካታችነትን በሁሉም አንጻር ለማረጋገጥ በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ እንደነበር ተናግረው፤ እንደማሳያነት 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን ከሚያስፈጽምባቸው ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ ልዩ ምርጫ ጣቢያ ተቋቁሞላቸው የመራጮች ምዝገባ ያደረጉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች እና ወታደራዊ ካምፖች እንዲሁም በድረ-ገጽ ላይ አማራጭ የመራጮች ምዝገባ ያከናወኑ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጠቅሰዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ ተማሪዎች የተሣተፉበት የክርክር እና የጥያቄና መልስ መድረክ ባሳለፍው ሣምንት መጠናቀቂያ ላይ አካሄደ። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የተካሄደውን የክርክር መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርድ ሥራ አመራር አባሉ ተክሊት ይመስል ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ወጣቶችን ያሣተፈ መሰል መድረክ መዘጋጀቱ ወጣቶች በሀገሪቱ የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እንዲሁም በማኅበረሰብ ጉዳዮች ንቁ ተሣትፎ እንዲያደርጉ የሚያበረታታና ግንዛቤ የሚፈጥር እንደሆነና ወደፊትም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተናግረዋል።
የቦርዱ የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ያስተባበረው በኢትዮጵያ የምርጫ ሥርዓት ዙሪያ ትኩረት ያደረገው ክርክር እንዲሁም በልዩ ሁኔታ የተካሄደው ጥያቄና መልስ ላይ የተሣተፉ ተከራካሪ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎችና ክርክሩን የታደሙ ተማሪዎች የክርክር መድረኩ ዜጎች በዕውቀት ላይ የተመሠረተ የምርጫ ተሳትፎ እንዲኖራቸው አስተዋፅዖ እንዳለው ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ለመከላከል የሚያስችል የአሠራር ሥርዓት (Standard Operating Procedure (SOP)) አፀደቀ። በአሠራር ሥርዓቱ ጥቃቱን በተመለከተ የትኞቹ ተቋማት ይመለከታቸዋል የሚለውን የባለድርሻ አካላት ልየታን ጭምር ያካተተ ሲሆን፤ ከነዚኽም ውስጥ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን፣ የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን፣ ለምርጫ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኅብረት፣ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት እና የኢትዮጵያ ሴት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ጥምረት ይጠቀሳሉ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ምርጫ መታዘብ ላይ ለተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በሥርዓተ-ፆታ እና አካታችነት እንዲሁም በምርጫ ወቅት ሊፈጸሙ የሚችሉ ጥቃቶችን አስመልክቶ ሥልጠና ሰጠ።
ለ43 የሀገር ውስጥ ታዛቢዎች የተሰጠው ሥልጠና በዋናነት ትኩረቱን ያደረገው በሥርዓተ-ፆታ ዕኩልነትና ማኅበራዊ አካታችነት እንዲሁም በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እንዴት ባለ ሁኔታ መለየትና በተገቢውን መንገድ በትዝብት ሪፖርቱ ውስጥ ማካተት እንደሚቻል የሚያስገነዝብ ሲሆን፤ በተጨማሪም በቦርዱ በሴቶች ላይ የሚደርሱ የሥነ-ልቦና፣ የአካል እና የዲጂታል ጥቃቶችን አስቀድሞ ለመከላከል እንዲሁም ፈጣን ምላሽ ለመስጠት እየተዘጋጀ ስላለው የጋራ የአሠራር መመሪያ እና የባለድርሻ አካላት ልየታን አስመልክቶ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከቦርዱ ዕውቅና አግኝተው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫን በመታዘብ ሥራ ላይ ለተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባሳለፍነው ሣምንት መጠናቀቂያ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ። የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ሜላትወርቅ `ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ በቅድመ ምርጫ ተግባራቱ በርካታ ሥራዎችን ሲሠራ እንደነበር፤ ከዚኽም ውስጥ በምርጫ መታዘብ ሥራ ላይ ለሚሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዕውቅና መስጠት አንዱ እንደሆነ አስታውሰው፤ ይኽም ከቅድመ ምርጫ እስከ ድኅረ-ምርጫ ያለውን ሦስቱንም የምርጫ ዑደቶች እንደሚያካትት ተናግረዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት፣ የክልል ርዕሰ መስተዳድሮችና የከተማ መስተዳድር ከንቲባዎች፣ የፌደራልና የክልል የፀጥታ ተቋማት አመራሮች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎችና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በተገኙበት ውይይት ማካሄዱን ተከትሎ የአካባቢዎቹን የፀጥታ ሁኔታ አስመልክቶ የተለያዩ ውይይቶችን በተለያየ ጊዜ ከባለድርሻ አካላት ጋር ሲያደርግ ቆይቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ተዓማኒና ሁሉን አካታች ለማድረግ የሚያስችለውን በርካታ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። በዚኽም አግባብ ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለሚወዳደሩ ሴት ፓለቲካ ፓርቲ እና የግል ዕጩዎች ሥልጠና ሰጥቷል።
ከሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ምርጫ በሚደረግባቸው በ13 ክልሎችና በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች በሚገኙ በ17 ከተሞች በተሰጠው ሥልጠና ላይ ከ1,731 በላይ ሴት ዕጩዎች የተሣተፉ ሲሆን፤ ዐላማውም ሴት ዕጩዎች በምርጫ ወቅት ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ፆታዊ ጥቃቶች መገለጫቸውና ምላሽ ስለሚሰጡበት ሕጋዊ አግባብ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ላይ በሚኖራቸው ተሣትፎና የዐደባባይ ላይ ንግግሮችን ሲያደርጉ ሊከተሏቸው ስለሚገቡ ሥነ-ዘዴዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ማስቻል ነው።