Skip to main content

የስራ ማስታወቂያ የቢሮ ኃላፊ

መግቢያ፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግሥቱ ምርጫን እንዲያስፈጽም እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎችን እንዲያስተዳድር ሥልጣን የተሰጠው ተቋም ነው፡፡ ይህን ኃላፊነቱን በብቃት እንዲወጣ ተቋሙን በአዲስ መልክ በሚወጡ ሕጎች መሠረት እንደገና ማደራጀት ተገቢና አስፈላጊ መሆኑ ታምኗል፡፡ ተቋሙን በአዲስ መልክ የማደራጀት ዋናው ዓላማ የተቋሙን ተዓማኒነት እና ብቃት ከፍ ማድረግ እንዲሁም ነፃ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ የሆነ ምርጫ ማካሄድ እንዲቻል ነው፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተማሪዎች የክርክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ አካሔደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መካከል ዜጎች ስለ ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ሂደቶች በቂ ግንዛቤ እንዲኖራቸዉ ማስቻል አንደኛዉ ነዉ፡፡ በመሆኑም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከሐበጋር ዲቤትስ (ደበበ ኃ/ገብርኤል ከተባለ የሕግ ቢሮ) ጋር በመተባበር ከተለያዩ ትምህርት ቤቶች በተወከሉ የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መሀከል የክርክር መድረክ በድሬደዋ ከተማ አካሄዷል፡፡ የክርክሩ ጭብጥም በሁለት ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን፡ ለኢትዮጵያ የሚሻለዉ የመንግስት ሥርዓት ፌደራላዊ ወይስ አሃዳዊ? እና ዴሞክራሲ ተመራጭ የፖለቲካ ሥርዓት ነዉ ወይስ አይደለም? በሚሉ ሀሳቦች ዙሪያ ነዉ፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የወጣቶች የክርክር መድረክን አዘጋጀ

የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኮሚኒቲ ሰስተነብል ዴቬሎፕመንት ኤይድ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በ 3 የተለያዩ ከተሞች ማለትም ወላይታ ሶዶ፥ ሆሳዕና እና ወልቂጤ የክርክር መድረክ አካሂዷል። ይህ የክርክር መድረክ በወላይታ ሶዶ ከተማ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፥ በሆሳዕና ከተማ ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ እንዲሁም በወልቂጤ ከተማ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደ ሲሆን የሕግ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲዎቹ ማህበረሰብ አባላት ተሳትፈዋል። ክርክሩም በዋናነት በምርጫ ፥ዲሞክራሲና በሰብአዊ መብቶች ዙሪያ ሲሆን ተማሪዎች በንድፈ-ኃሳብ ደረጃ የተማሯቸውን ፅንሰ-ሀሳቦች ተግባራዊ እንዲያደርጉ እድል ያመቻቸ መድረክ መሆኑ ተጠቅሷል።

Share this post

ቦርዱ የ6ኛውን ሀገር አቀፍ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ውጤት ይፋ አድርጓል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ያካሄደውን የ6ኛው ዙር ሀገር አቀፍ ቀሪና የድጋሚ ምርጫ ውጤት ሰኔ 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ አድርጓል።

የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ በተጠቀሱት አራቱ ክልሎች ውስጥ በሚገኙ 29 ምርጫ ክልሎች ስር በሚገኙ በ1218 ምርጫ ጣቢያዎች መካሄዱ የታወቀ ሲሆን ውጤት ይፋ በማድረጊያ መርኃ-ግብሩ ላይ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች (ተወካዮች)፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ያቀረቡአቸው ዕጩዎች፣ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች፣ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ኃላፊዎችና ተወካዮች፣ የሚዲያ አካላት፣ የፌዴራልና የክልል የጸጥታ አካላት እና ጥሪ የተደረገላችሁ እንግዶች ታዳሚ ነበሩ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴንተር ፎር ኢምፓዎርመንት ኢትዯጵያ አሶሲዬሽን ከተባለ የሲቪል ማህበር ድርጅት ጋር በመተባበር የክርክር መድረክ አካሄደ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል የተለያዩ ሲቪል ማህበራት ድርጅቶችን በማቀናጀት እና የተመረጡ ውጤታማ ዘዴዎችን በመጠቀም በምርጫ ዲሞክራሲያዊ ሂደት ፥ የዜጎች ተሳትፎና ተያያዥ ርዕሰ-ጉዳዮች ዙሪያ ት/ት እየሰጠ ይገኛል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ ሴንተር ፎር ኢምፓዎርመንት ኢትዯጵያ አሶሲዬሽን ከተባለ የሲቪል ማህበር ድርጅት ጋር በመተባበር ከግንቦት 24/2016 ጀምሮ በሦስት ዙር የተከፋፈለ የክርክር መድረክ በወላይታ ሶዶ፥ ወራቤ እና ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ ተማሪዎችን በማሳተፍ አካሂዷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ‘ውመን ኢን ማይስ ኢትዮጵያ’ ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር በዲሞክራሲያዊ ምርጫ ሂደት እና የሴቶች ተሳትፎ ላይ ያተኮረ የክርክር መድረክ በወላይታ ዞን የተለያዩ ከተሞች አካሄደ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መካከል አንዱ ዜጎች በእውቀት ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲደርጉ የስነ- ዜጋና መራጮች ትምህርትን ማዳረስ ነው። በመሆኑም ቦርዱ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም የመራጮች መረጃ እና ትምህርትን ወደ ማህበረሰቡ ለማድረስ ከተለያዩ ሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር በጋራ እየሠራ ይገኛል፡፡

Share this post