Skip to main content

የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት

ኅዳር 24 2012  

የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ የመጨረሻ ውጤት 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን በኅዳር 10 ቀን 2012 ዓ.ም. ያስፈጸመ ሲሆን ኅዳር 13 ቀን 2012 ዓ.ም. የመጀመሪያ ደረጃ ውጤት ማሳወቁ ይታወሳል፡፡ ቦርዱ ከመጀመሪያ ደረጃው ውጤት በማስከተል የእያንዳንዱን የምርጫ ጣቢያዎች ውጤት በዝርዝር በመገምገም፣ የድምር እንዲሁም ሌሎች የምርጫ ውጤት አለመጣጣም (discrepancies) ያለባቸውን ጣቢያዎች በማየት ውሳኔ አስተላልፎ የሚከተለውን የመጨረሻ ውጤት አሳውቋል፡፡ በመሆኑም በአጠቃላይ ድምፅ ከተሰጠባቸው 1,692 ምርጫ ጣቢያዎች እና ተጨማሪ 169 ድምፅ መስጫ ጣቢያዎች መካከል በ235 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ቦርዱ የተለያዩ የድምርና የውጤት አለመጣጣም ችግሮች (discrepancies) አግኝቷል፡፡

Share this post

ህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚነት ስለመመዝገብ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ ህዝበ ውሳኔ አፈጻጸም ሂደት፣ በህዝበ ውሳኔ አስፈጻሚነት የሰራችሁ እና የአዲስ አበባ መስተዳድር ፕብሊክ ሰርቪስ ያወጣውን መስፈርት የምታሟሉ በምርጫ ማስፈጸም ስራችሁ ምክንያት ብቻ የጊዜ ገደብ ያለፈባችሁ አስፈጻሚዎች

1. የአስፈጻሚነት ባጃችሁን
2. የ2010 ዓ.ም እና 2011 ዓ.ም ተመራቂነታችሁን የሚያሳይ የትምህርት ማስረጃችሁን
3. የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪነት መታወቂያ በመያዝ

ህዳር 17 እና 18 ቀን 2012 ዓ.ም ሳሪስ በሚገኘው የቦርዱ ማሰልጠኛ ማእከል በመገኘት መመዝገብ እንደምትችሉ እናሳውቃለን፡፡ ቦርዱ በነዚህ ሁለት ቀናት የተመዘገቡ አስፈጻሚዎችን ስም ዝርዝር ለአዲስ አበባ ፕብሊክ ሰርቪስ ቢሮ የሚያስተላልፍ ሲሆን በነዚህ ቀናት ያልተመዘገቡ አስፈጻሚዎችን ስም ለመላክ እንደማይገደደድ ለማሳሰብ ይወዳል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የተዛባ መረጃ ማስተካከያ

ኅዳር 8 ቀን 2012 ዓ.ም.   

ዋልታ ኢንፎርሜሽን ዛሬ ጠዋት በሠራው ዘገባ የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ የከተማው ነዋሪ 90 በመቶ ሻፌታን መምረጡ ተረጋገጠ በሚል የሠራው ዘገባ የተሳሳተ መረጃ ሲሆን ምክትል ከንቲባው የመራጮችን ተሳትፎንና ጸጥታን እንጂ የሕዝበ ውሳኔውን ውጤት የሚመለከት ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጡም። የምርጫ ውጤትን ማሳወቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኃላፊነት ብቻ መሆኑ እየታወቀ የሚዲያ አካላት የምርጫን ዓይነት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልጉ ዜናዎች ሲሠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ትኩረት እንዲያደርጉ እንዲህ ዓይነት የተሳሳቱ መረጃዎች ሰላምንና ደህንነት የሚያናጉ በመሆናቸው እና በወንጀልም ስለሚያስጠይቁ ጋዜጠኞች ከዚህ ዓይነት ተግባራት እንዲቆጠቡ ቦርዱ ያሳስባል። 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 

Share this post

የተሳሳተ መረጃ ጥቆማ

ኅዳር 8 ቀን 2012 ዓ.ም.   

ዋልታ ኢንፎርሜሽን ዛሬ ጠዋት በሠራው ዘገባ የሀዋሳ ከተማ ምክትል ከንቲባ የከተማው ነዋሪ 90 በመቶ ሻፌታን መምረጡ ተረጋገጠ በሚል የሀራው ዘገባ የተሳሳተ መረጃ ሲሆን ምክትል ከንቲባው የመራጮችን ተሳትፎንና ጸጥታን እንጂ የሕዝበ ውሳኔውን ውጤት የሚመለከት ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጡም፡፡

የምርጫ ውጤትን ማሳወቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኃላፊነት ብቻ መሆኑ እየታወቀ የሚዲያ አካላት የምርጫን ዓይነት ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልጉ ዜናዎች ሲሠሩ ከፍተኛ ጥንቃቄ እና ትኩረት እንዲያደርጉ እንዲህ ዓይነት የተሳሳቱ መረጃዎች ሰላምንና ደህንነት የሚያናጉ በመሆናቸው እና በወንጀልም ስለሚያስጠይቁ ጋዜጠኞች ከዚህ ዓይነት ተግባራት እንዲቆጠቡ ቦርዱ ያሳስባል፡፡

Share this post

ለሚዲያዎች በሙሉ የተደረገ ጥሪ

ኅዳር 7 ቀን 2012 ዓ.ም.   

ለሚዲያዎች በሙሉ የዛሬውን ሕዝበ ውሳኔ አስመልክቶ አጭር ማብራሪያ ከምሽቱ 1 ሰዓት ላይ በጊዜያዊው ማስተባበሪያ ስለሚሰጥ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የአዲሱ ምርጫ ሳጥን ስርጭት

ኅዳር 4 ቀን 2011 ዓ.ም.           

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአዲሱ የምርጫና የፓለቲካ ፓርቲዎች ህግ 1162/2012 አንቀጽ 56 መሠረት የሚጠቀምባቸው የነበሩትን የድምፅ መስጫ ኮሮጆዎች በሚያሳይ ቁስ በተሠራ የምርጫ ሳጥን በመቀየር ለሲዳማ ሕዝበ ውሳኔ አፈጻጸም ለመጠቀም በስርጭት ዝግጅት ላይ ይገኛል።

 

Share this post

ጥብቅ ማሳሰቢያ ለሚዲያዎች በሙሉ

ጥቅምት 27 ቀን 2012 ዓ.ም.

የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን ለመዘገብ የተዘጋጃችሁ እና የዘገባ ፍቃድ ለማግኘት የጠየቃችሁ የሚዲያ አካላት መታወቂያችሁን ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና መስሪያ ቤት እና ሀዋሳ የሚገኙ ሚዲያዎች ደግሞ ሀዋሳ ከሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ ማስተባበሪያ መውሰድ እንደምትችሉ እንገልጻለን። ከቦርዱ ለሚዲያ የተዘጋጀውን መታወቂያ ሳይዙ የምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ መገኘት የምርጫ እና የፓለቲካ ፓርቲዎችን ህግ ጥሰት ሲሆን የምርጫ ጣቢያዎችን በማወክ በህግ የሚያስጠይቅ መሆኑን አጥብቀን እናሳስባለን።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

Share this post

የውይይት መድረክን ስለመሰረዝ

ጥቅምት 26 ቀን  2012 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ሕዝበ ውሳኔን ሲያከናውን ዋና ዋና ከሆኑት የምርጫ ተግባራት መካከል አንዱ የሆነውን መራጮች የሚገባውን መረጃ እንዲያገኙ የሚያስችላቸውን የምርጫ ቅስቀሳ ቀናት አሳውቆ እንደነበር ይታወቃል። ከዚህም በተጨማሪም ለሲቪል ማህበራት እና ለፓርቲዎች ጥሪ በማድረግ አስፈላጊውን የቅስቀሳ መድረክ እንደሚያዘጋጅ ገልጾ እንደነበርም ይታወሳል።

Share this post

የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን በተመለከተ ለመገናኛ ብዙኃን በሙሉ የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሲዳማ ህዝበ ውሳኔን እያስፈጸመ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ በድርጊት መርሃ ግብሩ መሠረት የመራጮች ምዝገባ ጥቅምት 26 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ጀምሮ ኅዳር 6 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ይጠናቀቃል፡፡ ሕዝበ ውሳኔውም ኅዳር 1ዐ ቀን 2ዐ12 ዓ.ም ይከናወናል፡፡ ይህንን ሂደት መከታተል የሚፈልጉ እና ህጋዊ ምዝገባ ያላቸው የመገናኛ ብዙኃን እስከ ማክሰኞ ጥቅምት 25 ቀን 2ዐ12 ዓ.ም እስከ ቀኑ 11 ሰዓት ከ30 ድረስ ለሥራው የሚመድቡትን ጋዜጠኛ (ቢበዛ ሁለት) ስም በጽሁፍ በማሳወቅ ፍቃድ ጥያቄ ማቅረብ ይችላሉ፡፡ በመሆኑም ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 5ዐ1 ድረስ በመምጣት ወይም የደብዳቤውን ስካን ቅጂ በቦርዱ ኢሜይል electionsethiopia [at] gmail.com በመላክ ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ እናሳስባለን፡፡