Skip to main content

ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ላይ ለሚሣተፉ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ መታዘብ ሥነ-ዘዴን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስችለውን በርካታ የቅድመ-ዝግጅቶች ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከነዚኸም ውስጥ መራጮች እና ዕጩዎችን በቴክኖሎጂ በመታገዝ እንዲመዘገቡ የሚያስችል ሥርዓት መዘርጋት በዋናነት ተጠቃሽ ሲሆን፤ ይኽን እና መሰል ተግባራትን ሲያከናውንም የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ጨምሮ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀራርቦ በመሥራት ነው።

ቦርዱ በምርጫ መታዘብ ላይ ለሚሠማሩ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች የምርጫ መታዘብ ዕቅድ ዝግጅት እና የግኝት ሪፖርት አቀራረብ ሥነ-ዘዴ ላይ ያተኮረ ሥልጠና በትላንትናው ከትላንት በስትያ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ዓ.ም. ሰጠ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከናይጄሪያ አቻው Independent National Electoral Commission (INEC) ጋር የልምድ ልውውጥ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ ተግባራቱ የምርጫ አፈጻጸምን ያዘምናሉ ያላቸውንና ነፃና ተዓማኒነቱን፤ አሣታፊና ተደራሽነቱን ለማጎልበት የሚያግዙትን በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚኽም ውስጥ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለአፈጻጸም አስቸጋሪና ተግባራዊ ለማድረግ መሬት ላይ ካለው ተጨባጭ ሁነት ጋር መጣጣም ያልቻሉትን የሕግ ማዕቀፎች በባለሞያ አስጠንቶና ባለድርሻ አካላትን አማክሮ በማሻሻል ማፀደቅ፣ ተደራሽነቱንና አሣታፊነቱን ለማረጋገጥ የሚያግዙት ተጨማሪ ቅርንጫፍ ቢሮዎችን መክፈት፣ የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ ታግዞ በመመዝገብ ታዛቢዎችን ጨምሮ ለባለድርሻ አካላት በቀላሉ ለመለየት እንዲቻሉ የሚያስችል ሥራ መሥራት፣ ለምርጫና ለቢሮ ሥራ የሚያግዙ ቁሳቁሶችን ማሟላት እንዲሁን የቦርዱን ሠራተኞች ዐቅም የሚያጎለብቱ ሥልጠናዎችን በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ እንዲወስዱ ማስቻል ተጠቃሽ ናቸው። ቦርዱ ከላይ ከተጠቀሱት ተግባራት በተጨማሪም ከተለያዩ ሀገራት የምርጫ ቦርድ ተቋማት ጋርም እን

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ21ኛው ዓለም ዐቀፍ የምርጫ ቦርድ ተቋማት ሲምፖዚየም ሽልማት ተሸላሚ ሆነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቦትስዋና በተካሄደው በ21ኛው ዓለም ዐቀፍ የምርጫ ቦርድ ተቋማት ሲምፖዚየም ሽልማት የ Electoral Ergonomic Award Recognition for Outstanding Achievement ተሸላሚ ሆነ። ከመስከረም 22-23 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን ሲምፖዚየም Independent Electoral Commission of Botswana ከ International Centre for Parliamentary Studies (ICPS) ከተባለው ዓለም ዐቀፍ ተቋም ጋር በመተባበር ያዘጋጁት የዲሞክራሲያዊ ልኅቀት ማጎልበቻና የልምድ ልውውጥ ማድረጊያ ሲምፖዚየም ሲሆን፤ የተለያዩ ክፍላተ-ዓለም ሀገራት የምርጫ ቦርድ ተቋማት ኮሚሽነሮች ተሣትፈውበታል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት ፖለቲከኞች በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚኖራቸውን ተሣትፎ ለማሳደግ የሚያስችል የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሠጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተቋማዊ ኃላፊነቱን ሲወጣ ትኩረት ከሚሰጣቸው ተግባራት አንዱ የሥርዓተ-ፆታና ማኅበራዊ አካታችነት ተጠቃሽ ነው። ቦርዱ ሴት ፖለቲከኞች በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚኖራቸውን ተሣትፎ ለማሳደግ በማሰብ መስከረም 19-20 ቀን 2018 ዓ.ም. የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሠጠ፡፡ የመድረኩን መክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ሴቶችና እና አካል ጉዳተኞች በምርጫ ላይ የነቃ ተሣትፎና የጎላ ድርሻ እንዲኖራቸው የሚያበረታቱ ድንጋጌዎች በሕግ-ማዕቀፎቹ እንዲካተቱ ከማድረግ ባሻገር፤ በርካታ የዐቅም ግንባታ ሥልጠናዎችንና ድጋፎችን እየሰጠ እንደሚገኝ አስታውሰው፤ ይህም ሥልጠና በ7 ኛው ሀገራዊ ምርጫ የነቃ ተሣትፎ እንዲኖራቸው እንደሚያስችል ያላቸውን ዕምንት ገልጸዋል።

Share this post

ቦርዱ ዲጂታል የመራጮችና የዕጩዎች ምዝገባ ረቂቅ መመሪያዎች ላይ ከፓለቲካ ፖርቲዎች እንዲሁም ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተያዘው ዓመት በሚያካሂደው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ከሚያስተዋውቃቸው ዘመናዊ የምርጫ ሥርዓት ውስጥ አንዱ መራጮችና ዕጩዎች ኢንፍራስትራክቸር ባሉባቸው ቦታዎች በመሆን ራሳቸውን በራሳቸው በመራጭነት አልያም በዕጩነት እንዲመዘግቡ የሚያስችል የዲጂታል አማራጮች እንደሆኑ ይታወቃል። ቀደም ሲል ቦርዱ ያበለጸገውን በቴክኖሎጂ የታገዘ የመመዝገቢያ ሥርዓት ምን ዓይነት ሂደትን እንደሚከተል የአተገባበር ቅደም ተከተሉን ለፖለቲካ ፓርቲዎችና ለሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች በማሳየት ግብዓት የሰበሰበ ሲሆን፤ ሥራውን ለመሥራት የሚያስችለውን የተሻሻለውን ዐዋጅ ተከትሎም መመሪያ ማውጣት በማስፈለጉ ባሳለፍነው ሣምንት መስከረም 9 እና 10 ቀን 2018 ዓ.ም. ከፓለቲካ ፖርቲ ተወካዮች እንዲሁም ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች ጋር አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት በተገኙበት ምክረ-ሐሳብ መሰብሰቢያ ውይይት አኳሂዷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሥነ-ዜጋ እና ለመራጮች ትምህርት ክፍል ባለሙያዎቹ የዐቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በ2018 የሚያስፈጽመው 7ኛው ሀገራዊ ምርጫን አስመልክቶ እያከናወናቸው ከሚገኙ በርካታ ተግባራት ውስጥ የቦርዱን ባለሞያዎች ዐቅም የሚያጎለብቱ ሥልጠናዎችን መስጠት ይጠቀሳል። ቦርዱ ነሐሴ 28-29 ቀን 2017 ዓ.ም. ለዋናው መሥሪያ ቤትና ለቅርንጫፍ ጽ/ቤቶቹ የሥነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህረት ሥራ ክፍል ባለሞያዎቹ ሥልጠና ሰጠ። የሥልጠናውን የመክፈቻ ንግግር የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ተክሊት ይመስል ያደረጉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የሥልጣን ባለቤት ሕዝብ መሆኑን አስታውሰው የመራጮች ትምህርት መስጠቱም፤ የሥልጣን ባለቤት የሆነው ሕዝብ አስፈላጊው ግንዛቤ ኖሮት እንዲመርጥ እንደሚያስችለው ተናግረዋል። ይኽም ሲሆን በሥልጠናዎቹ አካታች መሆን መሠረታዊ ነገርና የግድ የሚል እንደሆነ አስገንዝበዋል።

Share this post

ቦርዱ በክርክር ክኅሎት ልምምድ ምንነት እና አተጋባበር ላይ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮቸን ያሣተፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ላይ በፓለቲካ ፖርቲዎች መካከል የሚካሄደው የፖሊሲ አማራጮ ክርክርን ታሳቢ ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ የተለያዩ ፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮችን ባሣተፈ መልኩ በትላንትናው ዕለት ነሐሴ 13 ቀን 2017 ዓ.ም. አካሄደ። ፖለቲካ ፓርቲዎች ሳይንሳዊ መንገድን ተከትለው ለመራጩ ሕዝብ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን እንዴት ባለ ሁኔታ ማቅረብ እንዳለባቸው ግንዛቤ ማስጨበጥ ዐላማው ያደረገውን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም መራጩ ሕዝብ በዕውቀት ላይ ተመሥርቶ እንዲወሥንና ድምፅ እንዲሰጥ ለማስቻል የመራጮች ትምህርትና የምርጫ ቅስቀሳ ማድረግ እንደሚያስፈልገው ሁሉ፤ በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የሚደረጉ ፖሊሲና ፕሮግራማቸውን የተመለከቱ ክርክሮችም እንዲሁ ወሣኝነት እንዳላቸው ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፖርቲዎችን የውስጥ አለመግባባት አፈታት ሥርዓታቸውን ለማጎልበት የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፖርቲዎች የውስጥ አለመግባባት አፈታት ስርዓታቸውን አጠናክረው እንዲተገብሩ የሚስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡

መልካም አስተዳደርን ለማጎልበት እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደትን ለማጠናከር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ ከነዚህም መካከል የፓለቲካ ፓርቲዎችን አቅም ማጎልበት ይገኝበታል፡፡ የስልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፖለቲካ ፓርቲዎች የውስጥ አለመግባባቶችን የሚፈቱበት ዘላቂነት ያለው ጠንካራ አደረጃጀት እና ሥርዓት ፈጥረው አለመግባባቶችን በውስጥ አቅማቸው ለመፍታት እንዲችሉ ለማድረግ ነው፡፡

Share this post