የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4/12 ምክር ቤት ጋር በመተባበር በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና በምርጫ ሂደት ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4/12 ምክር ቤት በተደረገለት ግብዣ መሰረት የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ክፍል ከቦርዱ አዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት እንዲሁም ከምርጫ ኦፐሬሽንስ የሥራ ክፍል ጋር በመቀናጀት ለሕፃናት ፓርላማ አባላትና ለባለድርሻ አካላት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የዜጎች መብትና ሃላፊነቶች፥ የኢትዮጵያ የምርጫ ሂደትን ከምርጫ ህጉ አኳያ እና በሕፃናት የፓርላማ አሰራር፥ አወቃቀርና መልሶ ማደራጀት ዙሪያ ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን ሥልጠና የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ሰጥቷል።