የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ የመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል ቦርዱ ከባለድርሻ አካላት ጋር መከረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገራችን የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ ሥርዓት በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ታግዞ ለማዘመን እንቅስቃሴ ጀምሯል።
በመጀመሪያ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል የታቀደው ሥራ በድሬደዋ ሁለት፣ በሐረሪ ሶስት፣ በሲዳማ አስራ ዘጠኝ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ሰባት የምርጫ ክልሎች ላይ እንደሚተገበር ታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ፤የሐረር እና የሲዳማ ክልሎች እና የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የክልል አስተዳደር አካላት፤ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የየክልሎቹ የምርጫ ላይዘን ኦፊሰሮች ታዳሚ ነበሩ::

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን የመረጃ ኃብቶች ለመጠበቅና ለመንከባከብ የሚያስችል ሥልጠና እየተሰጠ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ተቋማዊ ትውስታዎችን በመሰነድ ለትውልድ ማስተላለፍን ዓላማ ያደረገ ሥልጠና ከቦርዱ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች እየሰጠ ነው፡፡
ዘመናዊ የመረጃ አስተዳደርና የመረጃ ኃብቶች ጥበቃና እንክብካቤን በተመለከተ ከየካቲት 3 - 14 ቀን 2017ዓ.ም. በሚሰጠው ሥልጠና ሠልጣኞች ከምርጫ ጋር የተያያዙ የመረጃ ኃብቶች እንዴት እንደሚሰበሰቡ፣ እንደሚደራጁ እና እንደሚጠበቁ ጠለቅ ያለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያስችላል ተብሏል፡፡
በሥልጠናው መክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የታሪክ ጥበቃ ክፍላችን የበርካታ ሠነዶች እና መዛግብት ባለቤት በመሆኑ ለአጥኚዎች እና ተመራማሪዎች ጥናትና ምርምር ዕምቅ አቅም ያለው እና ሀገራዊ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ያሉንን መረጃዎች እና መዛግብት በአግባቡ አደራጅተን መጠበቅ ይገባናል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማሻሻል ላይ ያለው ዐዋጅ ረቂቅን በሲቭል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና በመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች አስተቸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር ቁጥር 1162/2011" ላይ ያደረገውን የዐዋጅ ማሻሻያ በተመለከተ ባሳለፍነው ሣምንት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ለመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በማቅረብ ማስተቸቱ ይታወቃል። ቦርዱ ይኽን ከባለድርሻ አካላት ጋር በረቂቅ ዐዋጁ ላይ የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሎ በተያዘው ሣምንትም ማለትም ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የረቂቅ ዐዋጅ ማሻሻያን ለሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶችና ለመገናኛ ብዙኃኑ አከላት ተወካዮች በማቅረብ ከተሣታፊዎቹ ሃሳብ አስተያየት ተቀብሏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ - የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 - የረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ላይ ምክረ ሃሳብ ለመሰብሰብ ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን ተወካዮች ጋር መከረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ላለፉት ስድሰት ዓመታት ስራ ላይ ያዋለውን የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ለማሻሻል በሁለት ዙሮች ለሁለት ቀናት በቆየ መርሃ-ግብር ከፓለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን አመራሮች ጋር በመወያየት ጠቃሚ ግብዓቶችን መሰብሰብ ቻለ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ