Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለቀድሞ የቦርዱ ሥራ አመራሮች የምስጋና ሽኝት እንዲሁም ለአዲስ ተሿሚዎች የእንኳን ደኽና መጣችሁ መርኅ-ግብር አካሄደ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ላለፉት ስድስት ዓመታት ያገለገሉት የቀድሞ የቦርድ ሥራ አመራር አባላት፤ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ፣ የቦርድ ሥራ አመራር አባላት ብዙወርቅ ከተተ እና ዶ/ር አበራ ደገፋ የምስጋና ሽኝት ሥነ-ሥርዓት፤ እንዲሁም የአዲስ ተሿሚ ሥራ አመራር አባላት፤ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ነዋይ፣ የቦርድ ሥራ አመራር አባላት ተክሊት ይመስል እና ነሲም አሊን የአቀባበል ሥነ-ሥርዓት ተካሂዷል።

የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ እና የቦርድ ሥራ አመራር አባሉ ፍቅሬ ገ/ሕይወት፣ የቀድሞ የቦርድ ሥራ አመራር አባላት ቤተሰቦች፣ የቦርዱ የዋናውና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሠራተኞች እንዲሁም ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት የተካሄደው የምስጋና ሽኝት መድረክ ላይ በርካታ የቀድሞ ሥራ አመራሮችን ስኬት የሚያሳዩ አጫጭር ዶክመንተሪዎች የታዩ ሲሆን፤ በቦርዱና በሥራ ባልደረቦቻቸውም የአክብሮትና የምስጋና መግለጫ ሽልማቶች ለቀድሞ አመራሮችና ለቤተሰቦቻቸው ተበርክቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሐረሪ ክልል ለሚገኙ የሐረር ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተያዘው በጀት ዓመት ካከናወናቸው በርካታ ተግባራት መካከል በተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ውስጥ ለሚገኙ የብሔራዊ ዩኒቨርስቲ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ስለምርጫ ሂደትና ስለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ በቂ ግንዛቤ እንዲያገኙ የሚያስችል ትምህርቶችንና መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ ይጠቀሳል። በተያዘው ወር ሥልጠናው ከተሰጣቸው በጎ-ፍቃደኛ ወጣቶች ውስጥ 25 የሐረሪ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች ሲኖሩበት፤ ቦርዱ ቀደም ሲል ከሰባት ዩኒቨርስቲዎች ለተውጣጡ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች፤ በያሉበት ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች ሆነው ሥልጠናውን እንዲወስዱ አድርጓል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የማኅበረሰብ ቲያትር በመቐለ ከተማ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመቐለ ከተማ በሚገኙት መቐለ ዩኒቨርስቲ ዓዲሓቂ ካምፓስ እና በደሳለኝ ሆቴል ለተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የማኅበረሰብ ቲያትር አቀረበ። የኪነ-ጥበብ ሥራው ከተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ለተውጣጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች አንዲሁም በትግራይ ክልል ለሚንቀሳቀሱ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የቀረበ ሲሆን፤ በተመሳሳይ መልኩ በመቐለ ዩኒቨርስቲ አዲ ሀቂ ካምፓስ ለሚገኙ ተማሪዎችም ቀርቧል።

ቦርዱ ፍኖት የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር ከተባለ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ቲያትር ዋና ዐላማ፤ሰላም ምርጫን ጨምሮ ለሁሉም ነገር መሠረት እንደሆነና እያንዳንዱ ዜጋ ሰላምን ለማስፈን ኃላፊነት እንዳለበት ግንዛቤ መፍጠር ሲሆን፤ በቀጣይም ፍኖት የሕግ ባለሙያዎች ማኅበር በትግራይ ክልል በተለያዩ አካባቢዎች ለሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች የኪነ-ጥበብ ሥራውን ለማቅረብ ዝግጅቱን አጠናቋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለጋምቤላ እና ለጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በጎ፟-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የሥነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት በመስጠት ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚኽም አማራጮች አንዱ በተለያዩ ክልሎችና ከተማ መስተዳድሮች በሚገኙ ብሔራዊ ዩኒቨርስቲዎች ለሚማሩ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ትምህርቱን በመስጠት በተዋረድ ለአካባቢያቸው ማኅበረሰብ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ ማስቻል ይጠቀሳል። ቦርዱ በያዝነው ወር ለጋምቤላ እና ለጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን የሰጠ ሲሆን፤ ቀደም ሲልም በአምስት የተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ በጎ-ፍቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን ሰጥቷል።

Share this post

ቦርዱ “የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት እና ሁሉን አካታች የምርጫ ተሣትፎ” የተሰኘ የማኅበረሰብ ቲያትር በአዳማ ከተማ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት እና ሁሉን አካታች የምርጫ ተሣትፎ” በሚል ርዕስ የማኅበረሰብ ቲያትር በአዳማ ከተማ በናፍያድ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት አካሄደ። ምርጫ ሁሉንም የማኅበረሰብ ክፍሎች የሚያካትት መሆኑንና አካል ጉዳተኛ ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸው የሚያስገኝላቸውን የመምረጥ መመረጥ መብታቸውን ተግባራዊ ከማድረግ ወደ’ኋላ ሊያስቀራቸው እንደማይገባ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ታስቦ በተዘጋጀው የማኅበረሰብ ቲያትር ላይ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች፣ መምህራን እንዲሁም የአስተዳደር ሠራተኞች የተሣተፉበት ሲሆን፤ ቲያትሩም በአማርኛና በአፋን ኦሮሞ ቋንቋዎች ቀርቧል። በቲያትሩ ላይ መስማት የተሳናቸው ተሣታፊዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በምልክት ቋንቋ እንዲከታተሉት ተደርጓል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለባሕር ዳር እና ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች በሥነ-ዜጋና በመራጮች ትምህርት ላይ ያተኮረ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች የሥነ¬-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ላይ የተሻለ መረዳት እንዲኖራቸው ለማስቻል በማሰብ በተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች ለሚገኙ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠና መስጠት መጀመሩ ይታወቃል። ቀደም ሲል ቦርዱ ለአዲስ አበባ፣ ለሰመራ እንዲሁም ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን የሰጠ ሲሆን፤ አሁን ደግሞ ለባሕር ዳር እና ለአሶሳ ዩኒቨርሲቲ በጎ-ፈቃደኛ ተማሪዎች ሥልጠናውን ሰጥቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሴት እና አካል ጉዳተኛ የፖለቲካ ፓርቲ አባላትና አመራሮች ፖለቲካዊ ተሣትፏቸውና የሚደርሱባቸው ተግዳሮቶችን የተመለከተ ሥልጠና ከሰኔ 1 እስከ ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለባለድርሻ አካላት አስተዋወቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቴክኖሎጂ የታገዘ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓት መተግበሪያውን ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች እንዲሁም ለሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች አስተዋወቀ። ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም. የተካሄደውን የማስተዋወቂያ መርኅ-ግብር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ማስፈጸሙ ተከትሎ የምርጫ ሥርዓቱን ለማዘመን ያግዛሉ ያላቸውን በርካታ ሥራዎች ሲሠራ መቆየቱን አስታውሰው፤ ከነዚኽም ውስጥ በባለድርሻ አካላት በተለያዩ ጊዜ አስተያየት ሲሰጥበት የነበረው ዘመናዊ የምርጫ አስተዳደር ሥርዓትን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ በመሥራት መራጮችና ዕጩዎች በቴክኖሎጂ ታግዘው የሚመዘገቡበትን መተግበሪያ ማበልጸጉን ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ “የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት" የተሰኘው መርኅ-ግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት” የተሰኘ መርኅ ግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አካሄደ። በተጠናቀቀው ግንቦት ወር 2017 ዓ.ም. ለተከታታይ ዘጠኝ ቀናት የተካሄደው መርሐ-ግብር ማስጀመሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤት የተካሄደ ሲሆን፤ በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉትን ከ74 በላይ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከግምት ውስጥ በማስገባትም በሥነ-ሥርዓቱ ላይ አካታችነትን የሚያስተምረውን ቲያትር መስማት ለተሳናቸው ታዳሚያን በቀጥታ ተተርጉሞ ቀርቧል።

Share this post

ቦርዱ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫን ተከትሎ በወሰዳቸው ሦስት ቁልፍ የምርጫ ሥርዓት ማዘመኛ ማሻሻያዎችን በተመለከተ ዎርክሾፕ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን መፈጸም ተከትሎ ሁሉምን ባለድርሻ አካላት፤ መገናኛ ብዙኃኑን ጨምሮ በተናጠል የስድስተኛው ሀገራዊ ምርጫን ስኬትና ተግዳሮት ተብለው ሊጠቀሱ የሚችሉትን ጉዳዮች በዝርዝርና በጥልቀት በመወያየት፤ የውይይቱንም ግኝት (Lesson Learned) ሁሉንም ባለድርሻ አካላት በአንድ ላይ ባሣተፈ መልኩ በድጋሚ አስተችቶ የማሻሻያ መፍትሔዎችን መውሰድን የቅድሚያ ቅድሚያ ተግባሩ አድርጎ ሲሠራ ቆይቷል።

ቦርዱ በባለድርሻ አካላት ማሻሻያ ተጠይቆባቸው የመፍትሔ ዕርምጃ ከወሰደባቸው ዋና ዋና አጀንዳዎች ውስጥ ለአፈጻጸም አስቸጋሪ የነበሩትን የዐዋጁ አንቀጾችን በመለየት ሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎችን እና ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮዎችን ባገናዘበ መልኩ የማሻሻያ ሃሳቦችን በባለሞያ አስጠንቶ ማቅረብ፣ የዕጩዎችንና የመራጮችን መጉላላት የሚያስቀር እና መረጃንም ዘመናዊ ሥርዓትን ጠብቆ ለማደራጀት የሚያግዝ የዲጂታይዜሽን ሥራ መሥራት ይጠቀሳሉ።

Share this post