የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ጥር 25 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የዕጩዎች ምዝገባን በምርጫ የጊዜ ሠሌዳው መሠረት ከጥር 1 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ቦርዱ ቀደም ሲል ባሳወቀው መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን ሙሉ በሙሉ በዲጂታል ሥርዓት ታግዘው በመመዝገብ ላይ ያሉ ሲሆን፤ ይኽንንም ለማከናወን እንዲችሉ የሲስተም አስተዳዳሪ ወኪሎቻቸውን ለቦርዱ አሳውቀው በሁለት ዙር ለአራት ቀናት ሥልጠና እንዲወስዱ አድርጓል። ሥልጠናውን ከመስጠት በተጨማሪ በስልክ እንዲሁም የሲስተም አስተዳዳሪዎችን ያካተተ “ቴሌግራም ግሩፕ” በመክፈትም በምዝገባ ወቅት ሊያጋጥሙ የሚችሉ ማንኛውንም ጥያቄዎቻቸውን ሲያስተናግድ ቆይቷል። ቦርዱ በተለያዩ አማራጮች የሲስተም አስተዳዳሪዎቹ የሚያከናውኑትን የዕጩዎች ምዝገባ ሲያስተባብር የነበረ ሲሆን፤ ከዛሬ ጥር 23 ቀን 2018 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና ከትምህርት ሚኒስቴር አመራሮች ጋር የመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የመራጮች ምዝገባ እና ድምጽ አሰጣጥን በሚመለከት ጥር 19 ቀን 2018 ዓ.ም ውይይት አደረገ፡፡
ውይይቱ የተካሄደው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ተስፋዬ ንዋይ፣ የዩኒቨርሲቲዎች ፕሬዚዳንቶች፣ የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንቶች እና የትምህርት ሚኒስቴር ተወካይ በተገኙበት ነው፡፡
የውይይቱ ዓላማ ከምርጫ ክልላቸው ርቀው በዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች ልዩ የምርጫ ጣቢያ ተዘጋጅቶላቸው በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚሳተፉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ያለመ ነው፡፡
ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስምንት ፖለቲካ ፓርቲዎች ጥር 15 ቀን 2018 ዓ.ም በጋራ ላወጡት መግለጫ የተሰጠ ምላሽ ሙሉ ይዘት ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ተኛውን ጠቅላላ ምርጫ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ለማከናወን በርካታ የቅድመ ምርጫ ተግባራት እያከናወነ ይገኛል። በመሆኑም ቦርዱ ምርጫ የሚያስፈጽሙ ገለልተኛ የምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችን በጊዜያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል።
በዚኽም መሠረት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መሥፈርቶች የምታሟሉ በሁሉም ክልሎች ላይ “በምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚነት” ማገልገል የምትፈልጉ አመልካቾች በሙሉ፤ ተከታዩን ማስፈንጠሪያ https://nebe-election.org/recruitment በመጠቀም ከታኅሣሥ 19 እስከ ታኅሣሥ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት እንድትመዘገቡ ቦርዱ ያሳውቃል። የምልመላ መሥፈርት፡-
ቦርዱ ኅዳር 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ባስተላለፈው ጥሪ፤ ፖለቲካ ፓርቲዎች “ቦርዱ ያበለጸገውን ሲስተም” ተጠቅመው ዕጩዎቻቸውን ለመመዝገብ እንዲችሉ “በቅድሚያ” ከጥሪው ጋር የተያያዙትን ቅጾች በመጠቀም የተጠየቁትን መረጃዎች አሟልተው ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ጥሪ ማስተላለፉ ይታወቃል።
የዕጩ ምዝገባ የሚከናወንበት አግባብ እና የቅጾች አጠቃቀም
1. የፖለቲካ ፓርቲ ቦርዱ ያበለጸገውን የዕጩ መመዝገቢያ ሲስተም ተጠቅሞ ዕጩ ለመመዝገብ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 እና የዕጩ ምዝገባ መመሪያ መሠረት በቅድሚያ የዕጩ ዝርዝር ማቅረቢያ ቅጽ አምስትን በመጠቀም የዕጩዎችን ዝርዝር መረጃ፤ የፓርቲውን ሊቀ-መንበር ሦስት የፊርማ ናሙና እና የመወዳደሪያ ምልክቱን ለቦርዱ አስቀድሞ ባሳወቀው ወኪል አማካኝነት ከኅዳር 8 እስከ ኅዳር 23 ቀን 2018 ዓ.ም. ለቦርዱ በአካል ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011” እና “በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011” መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል፡፡
በዚኹ መሠረት እነአቶ ጌታቸው ረዳ ካሕሳይ “ዴሞክራሲያዊ ስምረት ትግራይ (ስምረት) ወይም Tigray Democratic Solidarity Party (Solidarity)“ በሚል ስያሜ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ፤ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ 2 እና 3 መሠረት በፓርቲው ስም፣ ዐርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው፤ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ከጥቅምት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን ለቦርዱ ጽሕፈት ቤት እንዲያቀርብ ቦርዱ ያሳውቃል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ለሚታዘቡ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች በበይነ-መረብ አማካኝነት ምዝገባ እንዲያደርጉ እና መረጃ እንዲያደራጁ የሚያስችላቸውን የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሀ-ግብር ከጥቅምት 25-26 ቀን 2018 ዓ.ም. አካሄደ።
በበይነ-መረብ አማካኝነት የሚደረገው ምዝገባ እና የመረጃ አያያዝ ቀድሞ በተለምዷዊ ስርዓት ይከናወን የነበረውን አሰራር በዘመናዊ ስርዓት የቀየረ ነው። የግንዛቤ ማስጨበጫው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በበለጸገው የበይነ-መረብ መመዝገቢያ እና መረጃ መያዣው ላይ የራሳቸውን ግብዓት እንዲጨምሩበትም ያለመ ነው።
በበይነ-መረብ የሚደረገው ምዝገባ እና መረጃ አያያዝ፤ የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለማረጋገጥ እንደሚረዳ፣ በተገቢው ለመሰነድ እና የመረጃ ትንተና ለማዘጋጀት በእጅጉ ጠቃሚ እንደሆነ በመርሀግብሩ ላይ ተጠቅሷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ ሀገራት አቻ የምርጫ አስፈጻሚ ተቋማትን እና የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችን የተመለከተ ልዩ መርኃ-ግብር አካሄደ። አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት፣ የየሥራ ክፍልና የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እንዲሁም ከፍተኛ ባለሞያዎች በተሣተፉበት መድረክ ላይ፤ የተለያዩ ሀገራትን ምርጫዎች በመታዘብ ወቅት የተገኙ ልምዶችን እንዲሁም ከምርጫ አስፈጻሚ ተቋማት ጋር በተደረጉ የአቻ-ላቻ ልምድ ልውውጦች የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በተመለከተ በሁነቶቹ ላይ ተሣታፊ በነበሩ የቦርዱ ባለሞያዎች አማካኝነት ገለጻ ተሰጥቷል። በተወካዮቹ የቀረቡትን መልካም ተሞክሮዎች ተከትሎ በቡድን በቡድን በመሆን ከሀገራቱ ተሞክሮዎች ውስጥ ለኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ ተስማሚና ተፈጻሚ መሆን የሚችሉት የትኞቹ ናቸው የሚሉት ላይ በመወያየት ሃሳብ የቀረበ ሲሆን፤ የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችን በተመለከተም እንዲሁ አጭር ዘጋቢ ፊልም በማሳየት፤ ነባር የቦርዱ ባለሞያዎች ሊወሰዱ ይገባል ስላሏቸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የምርጫ ጊዜ ሠሌዳን በተመለከተ ከመገናኛ ብዙኃን እና ከሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶች ጋር በትላንትናው ዕለት ጥቅምት 17 ቀን 2018 ዓ.ም.