የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥነ-ዜጋ ትምህርት እና በምርጫ ዙሪያ የተዘጋጁ የኅትመት ውጤቶችን በሕዝብ ቤተ-መጻሕፍትና በተለያዩ ተቋማት የማሠራጨት ሥራ አከናወነ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በቦርዱ ማቋቋሚያ ዐዋጅ 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር የሥነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት እንደሚሰጥ እና እንደሚያስተባብር ይታወቃል። ይህውም መራጮች በቂ ምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙባቸውን የተለያዩ አማራጮች በመጠቀም ማለትም በኅትመት ውጤቶች (በበራሪ ወረቀቶች፣ በቡክሌት፣ በብሮሸሮች እና በሌሎች አማራጮች) ግንዛቤ የሚፈጥሩ መልዕክቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣ በቤተ-መጻሕፍት እንዲሁም በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ የማድረግ ሥራ ይሠራል። ቦርዱ ከላይ የተጠቀሰውን ኃላፊነት ለመወጣት በቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ክፍል አማካኝነት የግንዛቤ መስጫ ኅትመቶቹን በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬልም ጭምር እያዘጋጀ በማሠራጨት ላይ ይገኛል።
![](/sites/default/files/2023-11/photo_2023-11-01_00-28-52_1.jpg)