የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚያካሂደውን ሕዝበ ውሣኔ ለማስፈጸም ለተመለመሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚያካሂደውን ሕዝበ ውሣኔ ለማስፈጸም ለተመለመሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች የመራጮች ምዝገባ ማስፈጸም ተግባራትን የተመለከተ ሥልጠና ከታኅሣሥ 4 እስከ 10 ቀን 2015 ዓ.ም ሰጠ።
ሥልጠናው በስድስቱ ዞኖችና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች ላይ በሚገኙ 31 ማዕከላት ለሁለት ቀናት በተለያዩ ዙሮች የተሰጠ ሲሆን፤ ሥልጠናውም የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ የሚያስችሏቸውን መሠረታዊ የፅንሰ ሃሳብና የተግባር ልምምድ አካቷል ።