የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአሜሪካ ሰብአዊ ተራድኦ-የምርጫ እና የፓለቲካ ሂደቶችን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ድርጅቶች ጥምረት (USAID/CEPPS) እና ከአውሮፓ ህብረት-የአውሮፓ ምርጫ ነክ ሥራዎች ድጋፍ ማዕከል (EU/ECES) ጋር ውይይት አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአሜሪካ ሰብአዊ ተራድኦ-የምርጫ እና የፓለቲካ ሂደቶችን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ድርጅቶች ጥምረት (USAID/CEPPS) እና ከአውሮፓ ህብረት-የአውሮፓ ምርጫ ነክ ሥራዎች ድጋፍ ማዕከል (EU/ECES) ጋር የኢትዮጵያን የምርጫ ሥርዓት ሂደት ለማሻሻል የተደረጉ ድጋፎች ያስገኙትን ጠቀሜታ እና በቀጣይ ሊሰጡ በሚገቡ የድጋፍ ማዕቀፎች ዙሪያ ከተቋማቱ አስተባባሪ አካላት ጋር ውይይት አደረገ፡፡ የውይይቱ ዋነኛ ትኩረት ቀደም ሲል በልማት አጋሮቹ ሲሰጥ ለነበረው ድጋፍ እውቅና ለመስጠት እና በቀጣይም አጋዥ ተቋማቱ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማበረታታት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነው።