Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚያካሂደውን ሕዝበ ውሣኔ ለማስፈጸም ለተመለመሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚያካሂደውን ሕዝበ ውሣኔ ለማስፈጸም ለተመለመሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች የመራጮች ምዝገባ ማስፈጸም ተግባራትን የተመለከተ ሥልጠና ከታኅሣሥ 4 እስከ 10 ቀን 2015 ዓ.ም ሰጠ።

ሥልጠናው በስድስቱ ዞኖችና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች ላይ በሚገኙ 31 ማዕከላት ለሁለት ቀናት በተለያዩ ዙሮች የተሰጠ ሲሆን፤ ሥልጠናውም የመራጮች ምዝገባን ለማካሄድ የሚያስችሏቸውን መሠረታዊ የፅንሰ ሃሳብና የተግባር ልምምድ አካቷል ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ዎሕዴግ) ሐምሌ 23 ቀን 2014 ዓ.ም. ቦርዱ ያሳለፈዉ ዉሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ታኅሣሥ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ የዎላይታ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ዎሕዴግ) ሐምሌ 23 ቀን 2014 ዓ.ም. ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባዔ በሚመለከት ፓርቲው ከሪፖርት ጋር አያይዞ ያቀረባቸውን ሠነዶች ከሕጉ፣ ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ እና የቦርዱ ታዛቢዎች ካቀረቡት ሪፖርት አንጻር መርምሮ ውሣኔ አሣልፏል።

በውሣኔውም ፓርቲው ሐምሌ 23 ቀን 2014 ዓ.ም. ያሻሻለው መተዳደሪያ ደንቡ ላይ ከዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 ጋር የሚቃረኑ አንቀጾችን የለየ ሲሆን፤ አንቀጾቹ ተፈጻሚ እንዳይሆኑ እንዲሁም ጠቅላላ ጉባዔው በቀጣይ ስብሰባው አስፈላጊውን ማስተካከያ አድርጎባቸው ሪፖርት እንዲያቀርብ ሲል መወሠኑን ቦርዱ ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ አሳውቋል። የውሣኔውን ሙሉ ዝርዝር ደብዳቤዉ እዚህ ላይ ያገኙታል

የሕዝበ ውሣኔ ምልክት ስለመቀየር

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስድስቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ዎላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ እና ዲራሼ) በአንድ ክልል መደራጀታቸውን አልደግፍም ለሚለው የሕዝበ ውሣኔ አማራጭ ሃሣብ ነጭ ላም ምልክት ማድረጉ ይታወሳል፡፡

ይሁንና የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለቦርዱ የዚህ ሕዝበ ውሣኔ አማራጭ ምልክት ነጭ ላም መሆኑ ቀርቶ የደቡብ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል መስተዳድር ዐርማ የሆነው ጎጆ ቤት እንዲሆን ጥያቄ በማቅረቡ፤ ቦርዱም የምክር ቤቱን ጥያቄ ተቀብሎ ከላይ የተጠቀሱትን ስድስቱ ዞኖች እና አምስቱ ልዩ ወረዳዎች በአንድ የጋራ ክልል መደራጀታቸውን አልደግፍም ለሚለው የሕዝበ ውሣኔ አማራጭ ሃሣብ ምልክት ጎጆ ቤት እንዲሆን መወሠኑን ያሳውቃል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኅዳር 19 ቀን 2015 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ አስመልክቶ ለደ/ብ/ብ/ሕ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የፃፈዉ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኅዳር 19 ቀን 2015 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል ጉራጌ ዞን እዣ ወረዳ ፓርቲውን ወክለው በ6ኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫ ተወዳድረው የክልል ምክር ቤት አባል የሆኑትን አባሉ ኅዳር 17 ቀን 2015 ዓ.ም. አዲስ አበባ ከሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ተይዘው ወዳልታወቀ ቦታ መወሰዳቸውን፤ ኅዳር 20 ቀን 2015 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ ደ’ሞ በተያዙበት ወቅት አካላዊ ጉዳት ስለደረሰባቸው የሕክምና ዕርዳታ የሚያገኙበት መንገድ እንዲመቻች በመጠየቅ ለቦርዱ አቤቱታ ማቅረቡን ተከትሎ፤ ቦርዱም በዐዋጁ በተጣለበት ኃላፊነት መሠረት ለክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን በጉዳዩ ላይ ማብራሪያ እስከ ኅዳር 30 ቀን 2015 ዓ.ም. እንዲሰጠው አሳውቋል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ በሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ፤ የመራጮች ትምህርት በመስጠት ከሚሠማሩ የሲቪክ ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ምክክር እና የስልጠና መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኅዳር 27 ቀን 2015 ዓ.ም ከሲቪል ማኅበራቱ ጋር ያደረገውን ምክክር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ሕዝበ ውሣኔው በሚካሄድባቸው አካባቢዎች ላይ ድምፅ በመስጠት ለመሣተፍ ቅድመ ሁኔታውን የሚያሟሉ ዜጎች በነፃነትና በሰላማዊ መንገድ ፍላጎታቸውን የሚገልጹበትን ዲሞክራሲያዊ የምርጫ ዐውድ ለማረጋገጥ እንዲቻል ቦርዱ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር እየመከረ እንደሚገኝና በዕለቱም በመራጮች ትምህርት ላይ ከተሠማሩ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር የሚካሄደው ምክክር የዚሁ አንድ አካል እንደሆነ ተናግረዋል። የቦርድ አመራር አባል የሆኑት አበራ ደገፉ (ዶ/ር) በበኩላቸው ዜጎች በንቃት እንዲሣተፉና ፍላጎታቸውንም በነፃነት እንዲገልጹ ማሰተማር አሰፈላጊ መሆኑን ተናግረዋል። በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እና ቦርዱ እንዳዲስ ከተቋቋመ በኋላ በተካሄዱት ሁለቱ ሕዝበ ውሣኔዎች ላይ የሲቪል ማኅበራቱ እና የትምህርት ተቋማት የነበራቸው ሚና የላቀ እንደ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. የሚያካሂደውን ሕዝበ ውሣኔ ለማስፈጸም የተመለመሉ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ የመሥክ አሠልጣኞች ኅዳር 27-29 ቀን 2015 ዓ.ም. ሥልጠና ሰጠ

በቦርዱ የስልጠና ስራ ክፍል ለ299 የመሥክ አሠልጣኞች በሁለት ዙር የተሰጠው ሥልጠና በአርባ ምንጭ ከተማ የተካሄደ ሲሆን፤ ሥልጠናውም በሕዝበ ውሣኔው የመራጮች ምዝገባ ሂደት የተለያዩ ደረጃዎች ላይ የሚከናወኑ ተግባራትና ጥቅም ላይ የሚውሉ ቁሳቁሶችን የተመለከተ የንደፈ ሃሳብና የተግባር ልምምድ አካቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሳኔ በተለያየ የኃላፊነት ደረጃ ላይ ለሚሠማሩ አስተባባሪዎቹ ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሳኔ በተለያየ የኃላፊነት ደረጃ በሕዝበ ውሣኔው የዞን/ልዩ ወረዳ ማስተባበሪያ ጽ/ቤቶች እና ማስተባበሪያ ማእከላት ለሚሠማሩ አስተባባሪዎቹ ኅዳር 21 እና 22 ቀን 2015 ዓ.ም. በሁለት ዙር ሥልጠና ሰጠ።

Share this post

የሕዝበ ውሳኔው ጥያቄ እና ምልክቶች ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና በ5ቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ህዝበ ውሳኔ ለማካሄድ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። በዚሁ መሰረት ቦርዱ የህዝበ ውሳኔ ጥያቄ በተመለከተ ውሣኔ ሰጥቷል፡፡ ምልክቶችን የማስመረጥም ሂደት አከናውኗል፡፡

የሕዝበ ውሣኔው ጥያቄ አማራጮች፡-

1. “የ6ቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና 5ቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) በአንድ የጋራ ክልል መደራጀትን እደግፋለሁ” የሚለው ነው፡፡ ለዚህ ጥያቄ ምልክት ነጭ እርግብ በአስተዳደር ምክር ቤቶቹ ተመርጧል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ እነአቶ ዘለሌ ጸጋሥላሴ (19 ሰዎች) ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲን አስመልክቶ ያቀረቡትን የተለያዩ ቅሬታዎች ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ መርምሯል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ እነአቶ ዘለሌ ጸጋሥላሴ (19 ሰዎች) ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲን አስመልክቶ ያቀረቡትን የተለያዩ ቅሬታዎች ጥቅምት 28 ቀን 2015 ዓ.ም.