ቦርዱ አካል ጉዳተኞች በቀጣይ ምርጫዎች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው የዳሰሳ ጥናት እያስጠና መሆኑ ተገለፀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አካል ጉዳተኞች በ6ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የነበራቸውን ተሳትፎና ውክልና ምን ይመስል እንደነበረ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ በማስጠናት ላይ ይገኛል።
የዳሰሳ ጥናቱ ዋነኛ ዓላማ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የፓለቲካ ተሳትፎቸው ውስን እንዲሆን ያደረጓቸውን ችግሮች ነቅሶ በማውጣት በቀጣይ በሚኖሩ ምርጫዎች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው ቦርዱ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ምክረ ሃሳቦችን ለማመላከት ያለመ ነው።