የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ - የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 - የረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ላይ ምክረ ሃሳብ ለመሰብሰብ ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን ተወካዮች ጋር መከረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ላለፉት ስድሰት ዓመታት ስራ ላይ ያዋለውን የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ለማሻሻል በሁለት ዙሮች ለሁለት ቀናት በቆየ መርሃ-ግብር ከፓለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን አመራሮች ጋር በመወያየት ጠቃሚ ግብዓቶችን መሰብሰብ ቻለ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዱቤኔ ደጊኔ ነፃነት ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ውድቅ መደረጉን የወሰነበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዱቤኔ ደጊኔ ነፃነት ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ውድቅ መደረጉን የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የቦርዱን የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማስተባበሪያ ቢሮ የማቋቋም ፋይዳ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 በአንቀጽ 23 እና 24 መሠረት ቦርዱ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ምርጫ የሚያስተባብሩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንደሚያቋቁም ይደነግጋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልተማከለ የምርጫ አስተዳዳር ሥርዓቱ (Decentralized electoral administration) በምርጫ ዑደት ውስጥ ከቅድመ ምርጫ አንሥቶ እስከ ድኅረ ምርጫ ሒደቶች ድረስ ያሉትን ክንዋኔዎች ለህዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ይረዳው ዘንድ በቦርዱ ዋና መ/ቤት የሚገኝ ራሱን ችሎ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የሚያስተባብር የሥራ ክፍል አቋቁሟል፡፡
ቦርዱ ያዘጋጀውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋልን ለማዳበር የሚረዳ አውደ ጥናት ተካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ በአማካሪ ተቋም ያስጠናውን በ 2013 ዓ.ም. ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ሢሠራበት የነበረውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋል የሲቪል ማኅበራት ድርጅት አመራሮች፣ ተወካዮች፣ የቦርዱ የፌደራል እና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና የስነ-ዜጋና አካታችነት ባለሙያዎች በተገኙበት በመገምገም ሰነዱን የሚያዳብሩ ጠቃሚ ግብዓቶችን ሰበሰበ።
የቦርዱ የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ አተገባበር ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገለፀ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፉ አድርጎ ያስጀመረውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ስልታዊ ግቦች እና ዓላማዎች እንዲሳኩ በየደረጃው ያሉ የቦርዱ ሠራተኞችን ስለስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ይዘት እና አተገባበር ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተካሄዱ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአምስት ዓመቱ ስትራቴጂያዊ እቅድ ስኬታማነቱ የሚረጋገጠው እያንዳንዳችን የቦርዱ ሠራተኞች እና ኃላፊዎች በምናበረክተው ጉልህ አስተዋፅኦ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ለስትራቴጂያዊ ዕቅዱ እውን መሆን አሁን እያሳያችሁት ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፆታዊ ትንኮሳን የተመለከተ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት (procedure) ለሠራተኞቹ አስተዋወቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቴክኒክ ቡድን አዋቅሮ አንድ ዓመት በወሰደ ጊዜ ያስጠናውን የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት (procedure) በፌደራል እና በክልል ለሚሰሩ የቦርዱ ጏላፊዎችና ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ጥናት አስተዋወቀ።
በአውደ ጥናቱ በዋንኛነት የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት አስፈላጊነት፣ የፆታዊ ትንኮሳ ባህሪያት እና መገለጫዎች፣ የፆታዊ ትንኮሳ ክስ የሚቀርብበት ሥነ-ሥርዓት፣ የፓሊሲው የተፈፃሚነት ወሰን እና ፆታዊ ትንኮሳ በሚያስከትለው ችግሮች ላይ ገለፃ ተሰጥቶ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።