የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጋር የምስጋና እና የልምድ ልውውጥ አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ጋር የምስጋና እና የልምድ ልውውጥ መድረክ አካሄደ። ቦርዱ በ6ኛው ሀገራዊ የቀሪና ድጋሚ ምርጫ በአፋር፣ በቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ዜጎች ስለዴሞክራሲያዊ ምርጫ እና ሂደቶች ግንዛቤ እንዲጨብጡ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት እንዲያገኙ ብሎም በተለያዩ የስነ ዜጋ ትምህርት እሳቤዋች ዙሪያ ከተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር የክርክር መድረኮች በማዘጋጀት በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ሂደት የክርክር ባህል እንዲጎለብት የላቀ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የሲቪል ማኅበራቱ የምስጋና እና የልምድ ልውውጥ አካሂዷል።