የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጄንሲ አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በቂ የሆነ የሥነ-ዜጋ እና የምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ስልት በመቀየስና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት ከዋና ዋና ተግባራቱ መካከል አንዱ ነው፡፡ ቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ ይረዳው ዘንድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣ በህዝብ ቤተ-መጻሕፍት፣ በመንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ላይ ይገኛል።