የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካል ጉዳተኞችን አካታች ያደረገ የምርጫ ሂደትን የተመለከተ አውደ ጥናት አካሄደ
ምርጫ ቦርድ ከተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት /UNDP/ SEEDS PROJECT 2 ባገኘው ድጋፍ ከ ጥቅምት 18-20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የቆየ የአካል ጉዳተኞች በምርጫ ወቅት ሊኖራቸው የሚገባ ፍትሃዊ ተካታችነት የሚዳስስ አውደ ጥናት አካሄደ። አውደ ጥናቱ አካል ጉዳተኞችን ማእከል ያደረገ አሠራርን በምርጫ ሂደቶች እና ሥራዎች ውሰጥ ማቀድን እና አሁን በመተግበር ላይ ያሉ የምርጫ አሠራሮች ለአካል ጉዳተኞች ያላቸውን ተደራሽነት ለመገምገም የሚያስችል እውቀት እና ክህሎትን ለማሳደግ ያለመ ነበር።