Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጄንሲ አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በቂ የሆነ የሥነ-ዜጋ እና የምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ስልት በመቀየስና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት ከዋና ዋና ተግባራቱ መካከል አንዱ ነው፡፡ ቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ ይረዳው ዘንድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣ በህዝብ ቤተ-መጻሕፍት፣ በመንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየሠጠ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ የሥራ ክፍል አስተባባሪነት 45 ለሚሆኑ የቦርዱ የክልል ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የዲፓርትመንት ኃላፊዎች እና ኤክስፐርቶች በዕቅድ ዝግጅት (Planning)፣በጀት አያያዝ (Budgeting)፣ ክትትል እና ግምገማ (Monitoring and Evaluation)፣ የአፈጻጸም ሪፖርት አዘገጃጀት (Reporting)፤የሠራተኛ ምዘና (Performance Evaluation and Coach for Performance) ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየሠጠ ይገኛል፡፡

ከታህሣሥ 22 እስከ ታህሣሥ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ የሚቆየው ሥልጠና ዋና ዓላማ እያንዳንዱ ኃላፊ የሥራ ክፍሉን ተግባራት ለማቀድ፤በጀት ለመመደብ እና ደረጃውን የጠበቀ ሪፖርት ለማቅረብ የሚያስችለውን ዕዉቀት እና ክህሎት ለማስጨበጥ ያለመ ነው፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የሕትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣በህዝብ ቤተ- መጻሕፍት፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ እያደረገ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መሀከል መራጮች በቂ የምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ስልት መቀየስና በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርትን መስጠት አንዱ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ የሕትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣በህዝብ ቤተ- መጻሕፍት፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ እያደረገ ይገኛል።

Share this post

ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ

ከዚህ ቀደም ቦርዱን በሰብሳቢነት ሲመሩ የነበሩት ብርቱካን ሚደቅሳ ከነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን መልቀቃቸው ተከትሎ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል፡፡

ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ቀደም ብሎም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመሆን ከየካቲት 2012 ዓ.ም እስከ የካቲት 2015 ዓ.ም ማገልገላቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከወዲሁ ለወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው ይመኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ታህሣሥ 9 ቀን 2016 ዓ.ም.

Share this post

በስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ላይ ለሚሳተፉ የሲቪል ማህበራት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግስቱ እና በአዋጅ ቁጥር 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ የሲቪል ማህበራት ፍቃድ ይሰጣል።

የስነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት አስፈላጊነት ዜጎች በምርጫ ለመሳተፍ እና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ ለማድረግ በሚወስኑት ውሳኔ ላይ ተፅዕኖው በግልፅ ይታያል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም ይህንን ግብ እውን ለማድረግ የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎም አስፈላጊ ነው።

በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የክርክር መድረኮችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው ተቋማት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተማሪዎች እና ወጣቶች መካከል በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የክርክር መድረኮችን ለማዘጋጀ ፍላጎት ላላቸው ተቋማት ጥሪ ያቀርባል።

በመሆኑም ከዚህ በፊት ጥያቄ/ ማብራሪያ ያስገባችሁም ሆነ በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት እና ሚዲያዎች በተናጠል ወይም በጋራ የምርጫ ክርክር ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

ማንኛውም ክርክር ለማከናወን የሚያስብ ተቋም የሚመለከቱትን ዋና ዋና ነገሮችን ያሟላ የፍላጎት መግለጫ ሊያቀርብ ይገባል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለክልል ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ በሰራው የፍላጎት ዳሰሳ ግኝት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን አራተኛ ዙር ሥልጠና ለምርጫ ቦርዱ የክልል ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች “ምርጫ ነክ አለመግባባቶችን በምርጫ ሕጉ መሠረት በሚፈቱበት ሂደት፤ በአማራጭ የክርክር አፈታት ሂደቶች፤ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ በሚደርሱ ጥቃቶች እና በስርዓተ ጾታ እና አካታችነት” ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የቆየ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ከኀዳር 26 እስከ ኀዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ በቆየው ስልጠና ወደ 33 የሚደርሱ ከምርጫ ቦርድ የክልል ቅርጫፍ ጽ/ቤቶች የተውጣጡ የየቅርንጫፉ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳትፈዋል፡፡

ሥልጠናው ከምርጫ ቦርድ የሕግ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ጉዳዮች እና የስርዓተ ጾታ የሥራ ክፍሎች ባለሙያዎች እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን በምርጫ ቦርድ የሥልጠና ሥራ ክፍል አስተባባሪነት እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለሙያዎች ዘመናዊ የሪከርድና መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችላቸውን ስልጠና ወሰዱ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች በዶክመንቴሽን፣ በሪከርድ እና መረጃ አስተዳደር ርዕሰ ጊዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች አማካኝነት ከ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ የቆየ ስልጠና ተሰጥቷል።

አስር ቀን በቆየው ስልጠና በቦርዱ የሥራ ሂደት የሚሰበሰቡ ሪከርዶች ታሪካዊ ፋይዳቸው የላቀ በመሆኑ ሳይንሳዊ በሆነ ዘመናዊ የሪከርዶች አስተዳደር ስርዓት መደራጀት እና መጠበቅ እንዳለባቸው አፅንዖት ተሰጥቶታል፡፡

Share this post