የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን የመረጃ ኃብቶች ለመጠበቅና ለመንከባከብ የሚያስችል ሥልጠና እየተሰጠ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ተቋማዊ ትውስታዎችን በመሰነድ ለትውልድ ማስተላለፍን ዓላማ ያደረገ ሥልጠና ከቦርዱ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች እየሰጠ ነው፡፡
ዘመናዊ የመረጃ አስተዳደርና የመረጃ ኃብቶች ጥበቃና እንክብካቤን በተመለከተ ከየካቲት 3 - 14 ቀን 2017ዓ.ም. በሚሰጠው ሥልጠና ሠልጣኞች ከምርጫ ጋር የተያያዙ የመረጃ ኃብቶች እንዴት እንደሚሰበሰቡ፣ እንደሚደራጁ እና እንደሚጠበቁ ጠለቅ ያለ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ያስችላል ተብሏል፡፡
በሥልጠናው መክፈቻ መርሃ-ግብር ላይ መልዕክት ያስተላለፉት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የታሪክ ጥበቃ ክፍላችን የበርካታ ሠነዶች እና መዛግብት ባለቤት በመሆኑ ለአጥኚዎች እና ተመራማሪዎች ጥናትና ምርምር ዕምቅ አቅም ያለው እና ሀገራዊ ፋይዳ ያለው በመሆኑ ያሉንን መረጃዎች እና መዛግብት በአግባቡ አደራጅተን መጠበቅ ይገባናል ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በማሻሻል ላይ ያለው ዐዋጅ ረቂቅን በሲቭል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና በመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች አስተቸ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ "የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር ዐዋጅ ቁጥር ቁጥር 1162/2011" ላይ ያደረገውን የዐዋጅ ማሻሻያ በተመለከተ ባሳለፍነው ሣምንት ለሁለት ተከታታይ ቀናት ለፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ለመገናኛ ብዙኃን ተወካዮች በማቅረብ ማስተቸቱ ይታወቃል። ቦርዱ ይኽን ከባለድርሻ አካላት ጋር በረቂቅ ዐዋጁ ላይ የሚያደርገውን ውይይት ቀጥሎ በተያዘው ሣምንትም ማለትም ጥር 15 ቀን 2017 ዓ.ም. የረቂቅ ዐዋጅ ማሻሻያን ለሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅቶችና ለመገናኛ ብዙኃኑ አከላት ተወካዮች በማቅረብ ከተሣታፊዎቹ ሃሳብ አስተያየት ተቀብሏል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ - የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 - የረቂቅ አዋጅ ማሻሻያ ላይ ምክረ ሃሳብ ለመሰብሰብ ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን ተወካዮች ጋር መከረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ላለፉት ስድሰት ዓመታት ስራ ላይ ያዋለውን የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ለማሻሻል በሁለት ዙሮች ለሁለት ቀናት በቆየ መርሃ-ግብር ከፓለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች እና ከመገናኛ ብዙሃን አመራሮች ጋር በመወያየት ጠቃሚ ግብዓቶችን መሰብሰብ ቻለ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የኦጋዴን ብሔራዊ ነጻነት ግንባር (ኦብነግ) ታግዶ የማይሰረዝበትን መከላከያ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ እንዲያቀርብ የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዱቤኔ ደጊኔ ነፃነት ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ውድቅ መደረጉን የወሰነበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዱቤኔ ደጊኔ ነፃነት ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ውድቅ መደረጉን የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የቦርዱን የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ማስተባበሪያ ቢሮ የማቋቋም ፋይዳ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 በአንቀጽ 23 እና 24 መሠረት ቦርዱ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ምርጫ የሚያስተባብሩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንደሚያቋቁም ይደነግጋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልተማከለ የምርጫ አስተዳዳር ሥርዓቱ (Decentralized electoral administration) በምርጫ ዑደት ውስጥ ከቅድመ ምርጫ አንሥቶ እስከ ድኅረ ምርጫ ሒደቶች ድረስ ያሉትን ክንዋኔዎች ለህዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ይረዳው ዘንድ በቦርዱ ዋና መ/ቤት የሚገኝ ራሱን ችሎ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የሚያስተባብር የሥራ ክፍል አቋቁሟል፡፡