Skip to main content

የ6ኛው ዙር ቀሪና ድጋሚ ምርጫ እንዲሳካ የማስተባባር እና የክትትል ሥራ ያከናወኑ የክትትል ቡድኖች የሥራ ሪፓርት ተገመገመ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሰኔ13 ቀን 2013 ዓ.ም. እና መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. 6ኛውን ሀገር አቀፍ ምርጫ ማካሄድ በማይቻልባቸው ምክንያቶች ምርጫ ሳያካሂዱ በቀሩት በቤንሻንጉል-ጉሙዝ፣ አፋር፣ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ እና ሶማሌ ክልሎች የተካሄዱ የቀሪና ድጋሚ ምርጫዎች እንዳይስተጓጓሉ ድጋፍና ክትትል እንዲያደርጉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተዋቅረው፤ ስምሪት ተሰጥቷቸው የነበሩ 27 የክትትል ቡድኖችን የሥራ አፈፃፀም ሪፓርት የተገመገመበት መድረክ አካሄደ።

በመርሃ ግብሩ የማጠቃለያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የክትትል (Monitoring) ቡድን አደራጅተን ማሰማራት ከጀመርን ጊዜ አንስቶ የቦርዱ ምርጫ የማስፈፀም ዋነኛ ተልዕኳችን አይነተኛ መሻሻል አምጥቷል፤ በሂደቱም አሠራሮቻችንን ዳግም ለመፈተሽ በርካታ ትምህርቶችን መቅሰም ችለናል ብለዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአሜሪካ ሰብአዊ ተራድኦ-የምርጫ እና የፓለቲካ ሂደቶችን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ድርጅቶች ጥምረት (USAID/CEPPS) እና ከአውሮፓ ህብረት-የአውሮፓ ምርጫ ነክ ሥራዎች ድጋፍ ማዕከል (EU/ECES) ጋር ውይይት አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአሜሪካ ሰብአዊ ተራድኦ-የምርጫ እና የፓለቲካ ሂደቶችን የሚያጠናክሩ የተለያዩ ድርጅቶች ጥምረት (USAID/CEPPS) እና ከአውሮፓ ህብረት-የአውሮፓ ምርጫ ነክ ሥራዎች ድጋፍ ማዕከል (EU/ECES) ጋር የኢትዮጵያን የምርጫ ሥርዓት ሂደት ለማሻሻል የተደረጉ ድጋፎች ያስገኙትን ጠቀሜታ እና በቀጣይ ሊሰጡ በሚገቡ የድጋፍ ማዕቀፎች ዙሪያ ከተቋማቱ አስተባባሪ አካላት ጋር ውይይት አደረገ፡፡ የውይይቱ ዋነኛ ትኩረት ቀደም ሲል በልማት አጋሮቹ ሲሰጥ ለነበረው ድጋፍ እውቅና ለመስጠት እና በቀጣይም አጋዥ ተቋማቱ ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ ለማበረታታት የተዘጋጀ የውይይት መድረክ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) SEEDS ፕሮጀክት ያስገኘውን እና እያስገኘ ያለውን ፋይዳና ጠቀሜታ አስመልክቶ ውይይት አደረገ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) SEEDS ፕሮጀክት ያስገኘውን እና እያስገኘ ያለውን ፋይዳና ጠቀሜታ አስመልክቶ ከ UNDP SEEDS ፕሮጀክት አስተባባሪ አካላት፣ ከተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች እና ከልማት አጋር ድርጅቶች ተወካዮች ጋር ውይይት አደረገ።

የውይይቱ ዋነኛ ትኩረት ቀደም ሲል ለነበረው ድጋፍ እውቅና ለመስጠት እና ለነባር የ SEEDS ፕሮጀክት እና አዳዲስ አጋሮች ምርጫ ቦርድን እንዲደግፉ ለማበረታታት እና ስለ ምርጫ ቦርድ እድገት እና የትኩረት አቅጣጫዎች ለአጋር ድርጅቶች ለማስረዳት ያለመ ነበር።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፓለቲካ ፖርቲዎች የሴቶች እና የአካል ጉዳተኞችን የፓለቲካ ውክልና ለማጎልበት የሚሰጣቸው የማበረታቻ (የፋይናንስ) ድጎማ የውጤታማነት ደረጃ በዳሰሳ ጥናት ተገመገመ

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሠረት ቦርዱ ለፓለቲካ ፓርቲዎች እያደረገ ያለው የማበረታቻ ድጎማ ከአካታችነት አንፃር ለታለመለት ዓላማ መዋሉን እና ያስገኘውን ውጤት ለመገምገም የሚያስችል በአማካሪ ባለሙያ በተጠና የዳሰሳ ጥናት ላይ የእውቅና (Validation workshop) አውደጥናት አካሄደ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የፃፈዉ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም. ከጠቅላላ ጉባዔ፣ ከኦዲትና በሴት አባላት ቁጥር አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተገናኘ 11 ፓርቲዎች ላይ የዕግድ ውሣኔ ማሳለፉ ይታወቃል። ቦርዱ ከታገዱት ፓርቲዎች ውስጥ የይቅርታና የመከላከያ መልስ ያቀረቡትን አምስት ፓርቲዎች ጉዳይ መርምሮ፤ ፓርቲዎቹ ያለፈውን ስህተት እንደማይደግሙና በቀጣይም በሚያቀርቧቸው መረጃዎች ጥራት በመተማመን እንዲሁም የቦርዱን ሥራ ከሚያደናቅፍና ዕምነት ጥያቄ ውስጥ ከሚከቱ ተግባራት ተቆጥበው በሕግ አግባብ ብቻ እንደሚንቀሳቀሱ በማመን፤ በማስጠንቀቂያ ዕግዱን ያነሣ መሆኑን ያሳውቃል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ ስለነበረው የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ በታቀደው የዳሰሳ ጥናት መነሻ እቅድ ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ ስለነበረው የአካል ጉዳተኞች ውክልና እና ትርጉም ያለው ተሳትፎን በተመለከተ በምርጫ ቦርድ ለታቀደው የዳሰሳ ጥናት በቀረበ መነሻ እቅድ (Inception Plan) ላይ የምክክር መድረክ ኅዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. አካሄደ፡፡

የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ የዳሰሳ ጥናቱን እንዲሠሩ በቦርዱ ለተቀጠሩ አማካሪ ቡድኖች ጥናቱን ለማዳበር ግብዓት የሚሆን መረጃዎችን መሰብሰብ እና ባለድርሻ እና አጋር አካላት በጥናቱ ላይ የሚኖራቸውን ሚና ከፍ ማድረግ ነው፡፡

በውይይቱ ላይ ከተለያዩ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት፤ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ከጋራ ፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት፤ ከህብረት ለምርጫ፤ ከቦርዱ የተለያዩ ሥራ ክፍል የተውጣጡ ሠራተኞች እና ከጥናቱ አማካሪ ቡድን /Study Advisory Groups/ የተወከሉ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአንድ ዓመት በላይ ሲያስተባብር የነበረው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በተመረጡ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሲደረግ የነበረው ውይይት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአንድ ዓመት በላይ ሲያስተባብር የነበረው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በተመረጡ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚደረግ ውይይት መጠናቀቁን ኅዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም. አሳወቀ። አምስቱም የቦርዱ አመራር አባላት፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ-ሥላሴ፣ የውይይቱ ተሣታፊ የነበሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችና ታዛቢዎች፣ የውይይቱ መነሻ ሃሳብ የሚሆን ጥናት ያቀረቡ ባለሞያዎች እንዲሁም መገናኛ ብዙኃን የተገኙበትን የውይይቱን መጠናቀቅ ማብሰሪያ መርኅ-ግብር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም በታኅሣሥ 2011 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ሊደግፉ ከሚችሉ ለጋሽ ድርጅቶች ጋር የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፥ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች የድጋፍ ፕሮገራሞችን ከሚመሩ አጋሮች እና ሌሎች ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶችን ከሚደግፉ አጋሮች ጋር ኅዳር 28 ቀን 2024 ዓ.ም. የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት አካሄደ።

የውይይቱ ዓላማዎች የሚከተሉት ነበሩ፡-

Share this post

የኢትዮጵያ ሕፃናት ፓርላማ ምርጫ ሪፖርት

ዓለም አቀፍ የልጆች ቀን ለታዳጊ ትውልድ የተሻለና አስተማማኝ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስፈልገውን ትምህርት የማግኘት፣ ከጤና ጥበቃ እንዲሁም ሕጻናቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች እና መብቶች ጋር በተያያዘ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚረዳ መድረክ ሆኖ ያገለግላል። የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የልጆች ቀን ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ከተከበረባቸው ኩነቶች አንዱ የኢትዮጵያ ሕፃናትን ፓርላማን ምርጫ ማከናወን ነበር።

Share this post