Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ውጤት ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ላይ ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማዳመር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ ተደርገዋል።

Share this post

ቦርዱ የሚያካሂደውን የሕዝበ ውሣኔው ጊዜያዊ ውጤት የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ እንድትታዘቡ ጥሪ ስለማቅረብ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ላይ ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማመሳከር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶችን ለሕዝብ ይፋ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕዝበ ውሣኔውን ጊዜያዊ ውጤት ይፋ ማድረግ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (በኮንሶ፣ በደቡብ ኦሞ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ፣ በጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (በቡርጂ፣ በባስኬቶ፣ በአሌ፣ በአማሮ፣ በዲራሼ) ላይ ያካሄደው የሕዝበ ውሣኔ ድምፅ የመስጠት ሂደት መጠናቀቁን ተከትሎ፤ በምርጫ ጣቢያ ደረጃ ውጤት የማዳመር ሥራው ድምፅ በተሰጠባቸው ጣቢያዎች የተከናወነ ሲሆን፤ ውጤቱም ጥር 30 ቀን 2015 ከጠዋት ጀምሮ በየምርጫ ጣቢያዎች ለሕዝብ ይፋ ተደርጓል።

የተዳመረና የተመሳከረ ጊዜያዊ ውጤት በልዩ ወረዳ ደረጃ ይፋ ከተደረገባቸው ውስጥ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ እና ባስኬቶ ሲጠቀሱ፤ በዞን ደረጃ ደ’ሞ በኮንሶ ይፋ ተደርጓል። በተጠቀሱት ቦታዎች የጊዜያዊ ውጤቱ የማዳመርና ማመሳከር ሥራው ከጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም. እስከ የካቲት 1 ቀን 2015 ዓ.ም. ባለው ጊዜ የተሠራ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ዲራሼ) ላይ እያካሄደ ባለው የሕዝበ ውሣኔ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው መራጮች ድምጽ በመስጠት ላይ ይገኛሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ እያካሄደ ባለው የሕዝበ ውሣኔ ሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች ተከፍተው መራጮች ድምጽ በመስጠት ላይ ይገኛሉ

ቦርዱ በተለያዩ የመርጫ ጣቢያዎች ላይ እያደረገ ባለው ክትትል መሰረት የደረሰባቸው ግኝቶች እና የወሰዳቸው እርምጃዎች ከስር ተዘርዝረዋል

• 9 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የምርጫ ቁሳቁስ ጉድለት ሪፓርት የተደረገ ሲሆን ይህንኑ ለመቅረፍ በምርጫ ማእከል ደረጃ የማስተካከያ እርምጃ እየተወሰደ ይገኛል

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔ የመራጮች ድምጽ የመስጠት ሂደት እየተካሄደ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔ የመራጮች ድምጽ የመስጠት ሂደት እየተካሄደ ይገኛል፡፡

Share this post

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በነገው’ለት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ. ም. በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔው በድምፅ መስጫ ቀን አገልግሎት ላይ የሚውሉ ቁሳቁሶችን በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች አሠራጭቶ አጠናቀቀ

ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በነገው’ለት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ. ም. በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ለሚያካሂደው የሕዝበ ውሣኔው በድምፅ መስጫ ቀን አገልግሎት ላይ የሚውሉ ቁሳቁሶችን በሁሉም ምርጫ ጣቢያዎች አሠራጭቶ አጠናቀቀ።

Share this post

የቡሌ ምርጫ ክልል ድጋሚ ምርጫን ይመለከታል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ከሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ ጎን ለጎን በቡሌ ምርጫ ክልል ላይ የድጋሚ ምርጫ እንዲካሄድ በወሠነው መሠረት ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ምርጫው በጋራ እንደሚካሄድ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች እንዲደገም ውሣኔ በተላለፈባቸው ምርጫ ክልሎች ላይ በዚህ ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ በተለያዩ ምክንያቶች እንዲደገም ውሣኔ በተላለፈባቸው ምርጫ ክልሎች ላይ በዚህ ዓመት ምርጫውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ተግባራት እያከናወነ ይገኛል።

በዚሁ መሠረት በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በምቃንና ማረቆ ሁለት ምርጫ ክልል፣ በአፋር ክልል ደሉል ምርጫ ክልል እንዲሁም በቤኒሻንጉል ክልል መንጌ ምርጫ ክልል ላይ ለሚያካሂደው የድጋሚ ምርጫ፤ ምርጫውን የሚያስፈጽሙ ሠራተኞችን በጊዚያዊነት ለመቅጠር ይፈልጋል። ስለሆነም በተጠቁሱት አካባቢዎች ውስጥ የምትኖሩ በምርጫ አስፈጻሚነት በገለልተኝነት ማገልገል የምትፈልጉ እና ከፓርቲ አባልነት ነፃ የሆናችሁ አመልካቾች ከጥር 19 እስከ የካቲት 3 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ እንድታመለከቱ ቦርዱ ያሳውቃል።

የምልመላ መሥፈርት፡‐

• ዕድሜው/ዋ ከ18 ዓመት በላይ የሆነ/ች፣

• የማንኛውም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ያልሆነ/ች፣

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያካሄደው የመራጮች ምዝገባ አጠቃላይ አኅዛዊ መረጃ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ/ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ወላይታ፣ ጋሞ ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ በ3769 ምርጫ ጣቢያዎች ባካሄደው የመራጮች ምዝገባ ባጠቃላይ 3,028,770 የመራጮች ቁጥር የተመዘገበ ሲሆን፤ ከነዚህም ውስጥ 493 የአካል ጉዳተኞች ይገኙበታል።

አጠቃላይ የተመዝጋቢው ቁጥር በፆታ ሲገለጽ 1,575,371 ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 1,453,399 ሴቶች ናቸው። ከተመዘገቡት የአካል ጉዳተኞች ውስጥም እንዲሁ 296 ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 197 ሴቶች ናቸው። ከላይ የተመለከቱት አኅዞች ቀደም ሲል ቦርዱ ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ የመራጮች ቁጥር ላይ ባለመጠናቀቃቸው ያልተካተቱትን ጣቢያዎች እንዲሁም የድጋሚ ቆጠራ የተደረገባቸውን ጣቢያዎች ጭምር የያዘ ሲሆን፤ ድምር ውጤቱም በማዕከል ደረጃ የመጨረሻ የሚባለው የማረጋገጥ ሥራ የተከናወነበት ነው።

Share this post