Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአሶሳ ከተማ የወጣቶች ክርክር መድረክ አዘጋጀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በዴሞክራሲ ሥርዓት፣ የምርጫ ሂደት እንዲሁም ፖለቲካዊ እና ማኀበራዊ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ አካታች በሆነ መልኩ ለዜጎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ቦርዱ በሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በኩል "ኤሌክቶራል አክተርስ ሰፖርት ቲም" (EAST) ከተሰኘ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር ኅዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በአሶሳ ከተማ ከአሶሳ ዩኒቨርስቲ የተወጣጡ ተማሪዎችን ያሳተፈ የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን ቦርዱ ይህን መሰል የወጣቶች የክርክር መድረክ ሲያዘጋጅ ለ12ኛ ጊዜ ነው።

Share this post

የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት የተሳትፎ ጥሪ ማስታውቂያ

በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው ተቋማት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዜጎች በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ አካታች እና ተደራሽ የሆኑ የኪነጥበብ ሥራዎችን በተለይም የማህበረሰብ አቀፍ ቲአትር እና ሙዚቃ ነክ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ጥሪ ያቀርባል። በመሆኑም በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት እና ልምዱ ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት በተናጠል ወይም በጋራ በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማቅረብ ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) እንዲሁም የመተዳደሪያ ደንብ ቅጂ ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

Share this post

የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት የተሳትፎ ጥሪ ማስታውቂያ

በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው ተቋማት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዜጎች በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ አካታች እና ተደራሽ የሆኑ የኪነጥበብ ሥራዎችን በተለይም የማህበረሰብ አቀፍ ቲአትር እና ሙዚቃ ነክ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ጥሪ ያቀርባል። በመሆኑም በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት እና ልምዱ ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት በተናጠል ወይም በጋራ በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማቅረብ ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) እንዲሁም የመተዳደሪያ ደንብ ቅጂ ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአካል ጉዳተኞችን አካታች ያደረገ የምርጫ ሂደትን የተመለከተ አውደ ጥናት አካሄደ

ምርጫ ቦርድ ከተባበሩት መንግስታት የልማት ድርጅት /UNDP/ SEEDS PROJECT 2 ባገኘው ድጋፍ ከ ጥቅምት 18-20 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ የቆየ የአካል ጉዳተኞች በምርጫ ወቅት ሊኖራቸው የሚገባ ፍትሃዊ ተካታችነት የሚዳስስ አውደ ጥናት አካሄደ። አውደ ጥናቱ አካል ጉዳተኞችን ማእከል ያደረገ አሠራርን በምርጫ ሂደቶች እና ሥራዎች ውሰጥ ማቀድን እና አሁን በመተግበር ላይ ያሉ የምርጫ አሠራሮች ለአካል ጉዳተኞች ያላቸውን ተደራሽነት ለመገምገም የሚያስችል እውቀት እና ክህሎትን ለማሳደግ ያለመ ነበር።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወጣቶች የክርክር መድረክ በአርባ ምንጭ ከተማ አዘጋጀ፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እና የምርጫ ሂደት ዙሪያ ሁሉን ዜጎች አካታች የሆነ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየተገበረ ይገኛል። በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ከኤሌክቶራል አክተርስ ስፖርት ቲም (EAST) ከተባለ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር ጥቅምት15 ቀን 2017 ዓ.ም.

Share this post