የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች በበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በሁሉም የሀገሪቱ ክልሎችና ከተማ መስተዳደሮች በአካታችነት ለማዳረስ እንዲቻል በየክልሎቹና ከተማ መስተዳድሮቹ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች በጎ-ፍቃደኛ የሆኑ ወጣቶችን በመመልመል የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በመስጠት ሂደት ውስጥ ተሣታፊ እንዲሆኑ ዕቅድ ይዞ ለተግባራዊነቱ በትኩረት እየሠራ ይገኛል።