Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፓለቲካ ፖርቲዎች የሴቶች እና የአካል ጉዳተኞችን የፓለቲካ ውክልና ለማጎልበት የሚሰጣቸው የማበረታቻ (የፋይናንስ) ድጎማ የውጤታማነት ደረጃ በዳሰሳ ጥናት ተገመገመ

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሠረት ቦርዱ ለፓለቲካ ፓርቲዎች እያደረገ ያለው የማበረታቻ ድጎማ ከአካታችነት አንፃር ለታለመለት ዓላማ መዋሉን እና ያስገኘውን ውጤት ለመገምገም የሚያስችል በአማካሪ ባለሙያ በተጠና የዳሰሳ ጥናት ላይ የእውቅና (Validation workshop) አውደጥናት አካሄደ።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የፃፈዉ ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም. ከጠቅላላ ጉባዔ፣ ከኦዲትና በሴት አባላት ቁጥር አማካኝነት ከሚገኝ የገንዘብ ድጋፍ ጋር በተገናኘ 11 ፓርቲዎች ላይ የዕግድ ውሣኔ ማሳለፉ ይታወቃል። ቦርዱ ከታገዱት ፓርቲዎች ውስጥ የይቅርታና የመከላከያ መልስ ያቀረቡትን አምስት ፓርቲዎች ጉዳይ መርምሮ፤ ፓርቲዎቹ ያለፈውን ስህተት እንደማይደግሙና በቀጣይም በሚያቀርቧቸው መረጃዎች ጥራት በመተማመን እንዲሁም የቦርዱን ሥራ ከሚያደናቅፍና ዕምነት ጥያቄ ውስጥ ከሚከቱ ተግባራት ተቆጥበው በሕግ አግባብ ብቻ እንደሚንቀሳቀሱ በማመን፤ በማስጠንቀቂያ ዕግዱን ያነሣ መሆኑን ያሳውቃል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ ስለነበረው የአካል ጉዳተኞች ተሳትፎ በታቀደው የዳሰሳ ጥናት መነሻ እቅድ ላይ የምክክር መድረክ አካሄደ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ6ኛው አጠቃላይ የምርጫ ሂደት ላይ ስለነበረው የአካል ጉዳተኞች ውክልና እና ትርጉም ያለው ተሳትፎን በተመለከተ በምርጫ ቦርድ ለታቀደው የዳሰሳ ጥናት በቀረበ መነሻ እቅድ (Inception Plan) ላይ የምክክር መድረክ ኅዳር 30 ቀን 2017 ዓ.ም. አካሄደ፡፡

የምክክር መድረኩ ዋና ዓላማ የዳሰሳ ጥናቱን እንዲሠሩ በቦርዱ ለተቀጠሩ አማካሪ ቡድኖች ጥናቱን ለማዳበር ግብዓት የሚሆን መረጃዎችን መሰብሰብ እና ባለድርሻ እና አጋር አካላት በጥናቱ ላይ የሚኖራቸውን ሚና ከፍ ማድረግ ነው፡፡

በውይይቱ ላይ ከተለያዩ የአካል ጉዳተኞች ማህበራት፤ ከሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር፤ ከጋራ ፖለቲካ ፓርቲዎች ምክር ቤት፤ ከህብረት ለምርጫ፤ ከቦርዱ የተለያዩ ሥራ ክፍል የተውጣጡ ሠራተኞች እና ከጥናቱ አማካሪ ቡድን /Study Advisory Groups/ የተወከሉ አካላት ተሳትፈዋል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአንድ ዓመት በላይ ሲያስተባብር የነበረው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በተመረጡ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ሲደረግ የነበረው ውይይት ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአንድ ዓመት በላይ ሲያስተባብር የነበረው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል በተመረጡ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሚደረግ ውይይት መጠናቀቁን ኅዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም. አሳወቀ። አምስቱም የቦርዱ አመራር አባላት፣ የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረ-ሥላሴ፣ የውይይቱ ተሣታፊ የነበሩ ፖለቲካ ፓርቲዎችና ታዛቢዎች፣ የውይይቱ መነሻ ሃሳብ የሚሆን ጥናት ያቀረቡ ባለሞያዎች እንዲሁም መገናኛ ብዙኃን የተገኙበትን የውይይቱን መጠናቀቅ ማብሰሪያ መርኅ-ግብር በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም በታኅሣሥ 2011 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በምርጫ ወቅት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችን ሊደግፉ ከሚችሉ ለጋሽ ድርጅቶች ጋር የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፥ የሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች የድጋፍ ፕሮገራሞችን ከሚመሩ አጋሮች እና ሌሎች ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶችን ከሚደግፉ አጋሮች ጋር ኅዳር 28 ቀን 2024 ዓ.ም. የጠረጴዛ ዙሪያ ውይይት አካሄደ።

የውይይቱ ዓላማዎች የሚከተሉት ነበሩ፡-

Share this post

የኢትዮጵያ ሕፃናት ፓርላማ ምርጫ ሪፖርት

ዓለም አቀፍ የልጆች ቀን ለታዳጊ ትውልድ የተሻለና አስተማማኝ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስፈልገውን ትምህርት የማግኘት፣ ከጤና ጥበቃ እንዲሁም ሕጻናቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች እና መብቶች ጋር በተያያዘ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚረዳ መድረክ ሆኖ ያገለግላል። የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የልጆች ቀን ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ከተከበረባቸው ኩነቶች አንዱ የኢትዮጵያ ሕፃናትን ፓርላማን ምርጫ ማከናወን ነበር።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአሶሳ ከተማ የወጣቶች ክርክር መድረክ አዘጋጀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፣ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በዴሞክራሲ ሥርዓት፣ የምርጫ ሂደት እንዲሁም ፖለቲካዊ እና ማኀበራዊ በሆኑ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ አካታች በሆነ መልኩ ለዜጎች ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።

ቦርዱ በሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በኩል "ኤሌክቶራል አክተርስ ሰፖርት ቲም" (EAST) ከተሰኘ የሲቪል ማኀበረሰብ ድርጅት ጋር በመተባበር ኅዳር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. በአሶሳ ከተማ ከአሶሳ ዩኒቨርስቲ የተወጣጡ ተማሪዎችን ያሳተፈ የክርክር መድረክ ያዘጋጀ ሲሆን ቦርዱ ይህን መሰል የወጣቶች የክርክር መድረክ ሲያዘጋጅ ለ12ኛ ጊዜ ነው።

Share this post

የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት የተሳትፎ ጥሪ ማስታውቂያ

በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው ተቋማት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዜጎች በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ አካታች እና ተደራሽ የሆኑ የኪነጥበብ ሥራዎችን በተለይም የማህበረሰብ አቀፍ ቲአትር እና ሙዚቃ ነክ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ጥሪ ያቀርባል። በመሆኑም በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት እና ልምዱ ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት በተናጠል ወይም በጋራ በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማቅረብ ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) እንዲሁም የመተዳደሪያ ደንብ ቅጂ ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

Share this post

የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት የተሳትፎ ጥሪ ማስታውቂያ

በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው ተቋማት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዜጎች በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ አካታች እና ተደራሽ የሆኑ የኪነጥበብ ሥራዎችን በተለይም የማህበረሰብ አቀፍ ቲአትር እና ሙዚቃ ነክ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ጥሪ ያቀርባል። በመሆኑም በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት እና ልምዱ ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት በተናጠል ወይም በጋራ በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የኪነጥበብ ሥራዎችን ለማቅረብ ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) እንዲሁም የመተዳደሪያ ደንብ ቅጂ ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።