የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተጠናቀቀው ሣምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ተወያየ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ-መንግሥቱ ላይ በተቀመጠውና በቦርዱ ማቋቋሚያ ዐዋጀ ላይ በተደነገገው መሠረት ተጠሪነቱ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መሆኑ ይታወቃል፤ በዚኽም መሠረት ቦርዱ በተጠናቀቀው ሣምንት ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጋር ተወያይቷል። በውይይቱ ወቅትም ሁሉም የቦርድ አመራር አባላትና የጽ/ቤት ኃላፊዎች የተገኙ ሲሆን፤ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል፣ ግምገማና የመማማር ሥራ ክፍል ከፍተኛ ባለሞያ አማካኝነት ቦርዱ ለ7ኛው ሀገራዊ ምርጫ እያደረገ ያለውን ዝግጅን ጨምሮ እስካሁን የሠራቸውንና በመሥራት ላይ ያላቸውን ዋና ዋና ተግባራት በዝርዝር ቀርቧል።