የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ አስመልክቶ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የሕዝበ ውሣኔው ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ ባለሞያዎች ሥልጠና መሰጠት ጀመረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት በሚገኙ ስድስት ዞኖች (ኮንሶ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ዎላይታ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና አምስት ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ዲራሼ) ላይ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የድምፅ አሰጣጥ ሂደት የውጤት ማመሳከር፣ የማዳመርና ይፋ የማድረግ ሂደትን አስመልክቶ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የሕዝበ ውሣኔው ምርጫ አስፈጻሚዎችን ለሚያሠለጥኑ ባለሞያዎች ሥልጠና መሰጠት ጀመረ። በዚህ መሠረት እስካሁን የሚከተሉት ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል፦
- በሕዝበ ውሣኔ የድምፅ መስጫ ቀን የውጤት ማመሳከርና የማዳመር ሥልጠና ለመሪ አሠልጣኞች እና ለተወሠኑ የቦርዱ ኦፕሬሽን ክፍል ባልደረባዎች ጥር 4 እና ጥር 5 ቀን 2015 ዓ.ም. እንዲሁም ጥር 8 እና ጥር 9 ቀን 2015 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ተሰጥቷል።