የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ የመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል ቦርዱ ከባለድርሻ አካላት ጋር መከረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገራችን የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ ሥርዓት በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ታግዞ ለማዘመን እንቅስቃሴ ጀምሯል።
በመጀመሪያ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል የታቀደው ሥራ በድሬደዋ ሁለት፣ በሐረሪ ሶስት፣ በሲዳማ አስራ ዘጠኝ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ሰባት የምርጫ ክልሎች ላይ እንደሚተገበር ታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ፤የሐረር እና የሲዳማ ክልሎች እና የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የክልል አስተዳደር አካላት፤ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የየክልሎቹ የምርጫ ላይዘን ኦፊሰሮች ታዳሚ ነበሩ::
