በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ሲደረግ የነበረው የክርክር የተግባር ልምምድ መድረክ ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያዘጋጀውና ከጥቅምት 11 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ሲካሄድ የነበረው በፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል የነበረው የክርክር የተግባር ልምምድ መድረክ ተጠናቀቀ። ቦርዱ የ7ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ ለፖለቲካ ፓርቲዎች ለውይይት ማቅረቡን ተከትሎ መካሄድ የጀመረውና፤ ፖለቲካ ፓርቲዎች በምርጫ የክርክር ጊዜ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራማቸውን ለሕዝብ የሚያቀርቡበትን ሥልት እንዲያዳብሩበት ታስቦ የተዘጋጀውን መድረክ የመሩት፤ የሚዲያና የኮሚኒኬሽን ባለሞያ የሆኑት ብሌን ፍጹምና ጌታቸው ድንቁ (ፒ.ኤች.ዲ) ሲሆኑ፤ በእያንዳንዱ ክርክር ማጠቃለያ ላይ ባለሞያዎቹ ተከራካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ የተከተሉት የክርክር ሥነ-ዘዴን ጠንካራና ደካማ ጎን በመለየት ሞያዊ ምክረ ሃሳብ አቅርበዋል።