የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፖርቲዎችን የውስጥ አለመግባባት አፈታት ሥርዓታቸውን ለማጎልበት የሚያግዝ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀመረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፓለቲካ ፖርቲዎች የውስጥ አለመግባባት አፈታት ስርዓታቸውን አጠናክረው እንዲተገብሩ የሚስችል የአቅም ግንባታ ስልጠና መስጠት ጀመረ፡፡
መልካም አስተዳደርን ለማጎልበት እና የዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ሂደትን ለማጠናከር የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡ ከነዚህም መካከል የፓለቲካ ፓርቲዎችን አቅም ማጎልበት ይገኝበታል፡፡ የስልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፖለቲካ ፓርቲዎች የውስጥ አለመግባባቶችን የሚፈቱበት ዘላቂነት ያለው ጠንካራ አደረጃጀት እና ሥርዓት ፈጥረው አለመግባባቶችን በውስጥ አቅማቸው ለመፍታት እንዲችሉ ለማድረግ ነው፡፡