የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሶማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ ያደረገውን ጠቅላላ ጉባኤ ተቀብሎ ያፀደቀው መሆኑን የገለፀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የዱቤኔ ደጊኔ ነፃነት ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ውድቅ መደረጉን የወሰነበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ
የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 1133/2011 በአንቀጽ 23 እና 24 መሠረት ቦርዱ በሁሉም የሀገራችን ክልሎች ምርጫ የሚያስተባብሩ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች እንደሚያቋቁም ይደነግጋል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባልተማከለ የምርጫ አስተዳዳር ሥርዓቱ (Decentralized electoral administration) በምርጫ ዑደት ውስጥ ከቅድመ ምርጫ አንሥቶ እስከ ድኅረ ምርጫ ሒደቶች ድረስ ያሉትን ክንዋኔዎች ለህዝብ ተደራሽ የሆነ አገልግሎት ለመስጠት ይረዳው ዘንድ በቦርዱ ዋና መ/ቤት የሚገኝ ራሱን ችሎ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን የሚያስተባብር የሥራ ክፍል አቋቁሟል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ በአማካሪ ተቋም ያስጠናውን በ 2013 ዓ.ም. ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ሢሠራበት የነበረውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋል የሲቪል ማኅበራት ድርጅት አመራሮች፣ ተወካዮች፣ የቦርዱ የፌደራል እና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና የስነ-ዜጋና አካታችነት ባለሙያዎች በተገኙበት በመገምገም ሰነዱን የሚያዳብሩ ጠቃሚ ግብዓቶችን ሰበሰበ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 7 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፉ አድርጎ ያስጀመረውን የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ስልታዊ ግቦች እና ዓላማዎች እንዲሳኩ በየደረጃው ያሉ የቦርዱ ሠራተኞችን ስለስትራቴጂያዊ ዕቅዱ ይዘት እና አተገባበር ግንዛቤ እንዲኖራቸው የሚያስችሉ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች ተካሄዱ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአምስት ዓመቱ ስትራቴጂያዊ እቅድ ስኬታማነቱ የሚረጋገጠው እያንዳንዳችን የቦርዱ ሠራተኞች እና ኃላፊዎች በምናበረክተው ጉልህ አስተዋፅኦ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ለስትራቴጂያዊ ዕቅዱ እውን መሆን አሁን እያሳያችሁት ያለውን ቁርጠኝነት አጠናክራችሁ እንድትቀጥሉ ይጠበቃል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቴክኒክ ቡድን አዋቅሮ አንድ ዓመት በወሰደ ጊዜ ያስጠናውን የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት (procedure) በፌደራል እና በክልል ለሚሰሩ የቦርዱ ጏላፊዎችና ሠራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ጥናት አስተዋወቀ።
በአውደ ጥናቱ በዋንኛነት የፆታዊ ትንኮሳ ፓሊሲ እና የማስተግበሪያ ሥነ-ሥርዓት አስፈላጊነት፣ የፆታዊ ትንኮሳ ባህሪያት እና መገለጫዎች፣ የፆታዊ ትንኮሳ ክስ የሚቀርብበት ሥነ-ሥርዓት፣ የፓሊሲው የተፈፃሚነት ወሰን እና ፆታዊ ትንኮሳ በሚያስከትለው ችግሮች ላይ ገለፃ ተሰጥቶ ሰፊ ውይይት ተደርጓል።
የተባበሩት መንግስታት የልማት ፕሮገራም /United Nations Development Program-UNDP /ለምርጫ ቦርድ በሚሰጠው የ(SEEDS2) ፕሮጀክት ድጋፍ እኤአ በ2025 ዓመት ሊሠሩ የታሰቡ ሥራዎችን ለማቀድ በተካሄደው አውደ ጥናት ላይ ከቦርዱ የተለያዩ የሥራ ክፍሎች የተውጣጡ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ተሳትፈዋል፡፡ የአውደ ጥናቱ ዋና ዓላማም የቦርዱ ሥራ ክፍሎች ከUNDP (SEEDS2)ፕሮጀክት የሚያገኟቸውን ድጋፎች ተከትሎ የሚሠሯቸውን ሥራዎች በተገቢው መንገድ እንዲያቅዱ ማስቻል እና የምርጫ ቦርድን የሥራ ዕቅድና የዕቅድ አፈፃፃም ተቋማዊ አቅምን ለማሳደግ ያለመ ነበር፡፡
የኢትዮጽያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የጋምቤላ ብሔራዊ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጋ.ብ.ዲ.ን) በኢትዮጽያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጁ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 78 (1(ሀ፣ለ)፣4) እንዲሁም አንቀጽ 79(1) ላይ የተመለከቱትን ድንጋጌዎች በመጣሱና በቂ መከላከያም ባለማቅረቡ፤ ቦርዱ በዐዋጁ አንቀጽ 68(7) በተሰጠው ሥልጣን መሠረት አንቀጽ 98 (1(ሠ))ን ጠቅሶ ፓርቲው መሠረዙን ያሳወቀበት ደብዳቤ ከታች ተያይዟል።
የኢትዮጽያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ታኅሣሥ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. በሥራ ላይ ያለው “የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011” የተመለከተ የሕግ ማሻሻያ ዐውደ ጥናት አካሄደ።
አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት፣ የየሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች እንዲሁም የቦርዱ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች የተገኙበትን ዐውደ-ጥናት በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ስድስተኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫን ተከትሎ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተካሄዱ የድኅረ-ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶች ግምገማ መድረክ ላይ የተነሡትን የሕግ ማሻሻያ የሚፈልጉ ዐዋጁ ላይ ያሉ ድንጋጌዎች ፤ ከሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ቀደም ብሎ በመለየት፤ ዓለም ዐቀፍ መመዘኛዎችን ባማከለና የተሻለ አፈጻጸምና ግልጸኝነትን ለማጎልበት እንዲረዳ ተደርጎ ማሻሻያ እንደተደረገበት ተናግረዋል።