የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁለተኛ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በዲጂታል ሲስተም የመመዝገብ ሥራ ማከናወን ጀመረ
የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት 2011 ዓ.ም. አንሥቶ አንድ ሀገራዊ ምርጫ እና ሦስት ሕዝብ ውሣኔዎችን ማስፈጸሙ ይታወቃል። ቦርዱ በቀጣይም የ7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እንደ አዲስ ከተቋቋመበት 2011 ዓ.ም. አንሥቶ አንድ ሀገራዊ ምርጫ እና ሦስት ሕዝብ ውሣኔዎችን ማስፈጸሙ ይታወቃል። ቦርዱ በቀጣይም የ7ኛውን ዙር ሀገራዊ ምርጫ ለማከናወን የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ከሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች (ሲ.ማ.ድ) ጋር የሚኖር የአጋርነት መድረክ አስፈላጊነት ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ። ውይይቱን በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ምርጫ ቦርድ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ምርጫን በተመለከቱ ጉዳዮች ላይ ለሚኖራቸው ተሣትፎ ዕውቅና ከመስጠት አንሥቶ አብሮ እስከመሥራት የደረሰ ግንኙነት እንዳለው አስታውሰው፤ ይኽም ሲሆን ሚናን በመለየት ተባብሮ መሥራቱ የምርጫን ነፃና ገለልተኛ እንዲሁም ዲሞክራሲያዊነቱን በማረጋገጥ ረገድ ከፍ ያለ አስተዋፅዖ ያለው በመሆኑ እንደሆነ ተናግረዋል። በዚኽም መድረክ ላይ ማኅበራቱ በምርጫ ትምህርትም ላይ ባላቸውም ተሣትፎ ይሁን እንደታዛቢ በሚኖራቸው ኃላፊነት መሻሻል የሚገባቸውን እየለዩ መሄድና የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከኔዘርላንድ የመድብለ ፓርቲ የዲሞክራሲ ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ከተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለተውጣጡ ፓለቲከኞች በምርጫ ክርክር ክህሎት ላይ ስልጠና እየሰጠ ይገኛል።
የሥልጠናው ዋንኛ ዓላማ ፓለቲከኞች ለመራጩ የሚያቀርቡት ማኒፌስቶ (ፓሊሲዎችና ፕሮግራሞች) የህዝብ ቅቡልነት እንዲያገኙ የፓለቲከኞች የምርጫ ክርክር ክህሎትን ማሳደግ ላይ ያተኮረ ነው።
በምርጫ ክርክር አማካኝነት ተፎካካሪ የፓለቲካ ፓርቲዎች ለመራጩ ህዝብ በሚሰጡት አማራጭ የፓሊሲ አማራጮች ምክንያት መራጮች ዕውቀት ላይ ተመስርተው የሚበጃቸውን እንዲመርጡ ከማስቻሉ ባሻገር የዲሞክራሲ ተሳትፎ ባህልን ይጎለብታል።
እነ ዶሪ አስገዶም ዓሲምባ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ/ዓዴፓ/ በሚል ስያሜ በ26/2/2012 ዓ.ም የክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ ህጋዊ የእውቅና ጥያቄ ለቦርዱ አቅርበው በምዝገባ ሂደት ላይ የነበሩ ሲሆን፤ የፓርቲው ህጋዊ የእውቅና ፈቃድ ሂደት በአገራችን በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ ቆይቶ በኋላም እነ ሐጎስ ወልዱ በቁጥር ዓዴ-0027/15 በቀን 25/07/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ተቋርጦ የነበረው ሂደት እንዲቀጥል በማለት አመልክተዋል፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ በድጋሚ በቁጥር ዓዴ-0032/15 በቀን 16/09/2015 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ጊዜያዊ የእውቅና ፈቃድ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡
የቦርዱ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን ለሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል ተደራሽ ለማድረግ ከተለያዩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ሌሎች አጋር አካላት ጋር በጋራ እየሰራ ይገኛል።
ትምህርቱን በመላው ሀገሪቱ በስፋት ተደራሽ ለማድረግ የበጎ ፈቃደኝነት አገልግሎት የሚሰጡ ወጣቶችን ከየክልሉ በመመልመል በየአካባቢያቸው ለማሰማራት እቅድ የያዘ ሲሆን በቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል ከሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ለተውጣጡ 25 የሁለተኛ እና ሦስተኛ ዓመት ተማሪዎች ከሚያዝያ 4 እስከ 5 /2017 ዓ.ም የቆየ የሁለት ቀናት የመጀመሪያ ዙር ስልጠና ሰጥቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በአካታችነት ማዕቀፍ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በ7ኛው ሀገር አቀፍ ጠቅላላ ምርጫ በመራጭነት እና በተመራጭነት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ምቹ ሁኔታዎችን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።
ይህን ዕቅድ ዕውን ለማድረግ ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን የምርጫ ፍላጎት ለመለየት እና ተሳትፎ ለማሳደግ ኢስት አፍሪካ የተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ቀጥሮ ሀገራዊ ጥናት በማስጠናት ላይ ይገኛል።
አጥኚ ድርጅቱ አጥንቶ ባቀረበው ረቂቅ የጥናቱ ግኝቶች ላይ ለመወያየት በተዘጋጀ የአንድ ቀን አውደ ጥናት ላይ መልዕክታቸውን ያስተላለፉት የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮችን በምርጫ ሂደት የማሳተፍ ትርጉም ያለው ስራ የቦርዱ ጏላፊነት ብቻ ሳይሆን፤ መንግስትን ጨምሮ የሁሉም ባለድርሻ አካላት ቅንጅታዊ አሠራር እና ትብብርን ይጠይቃል ብለዋል።
የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ባለሙያ በጋራ በመሆን በስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ዙሪያ ከቦርዱ ጋር እየሰሩ ለሚገኙ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እንዲሁም ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለተውጣጡ የተማሪ ተወካዮች ትምህርቱን በክልሉ ለሚገኙ ልዩ ልዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች በስፋት ማዳረስ ስለሚቻልበት ዘዴ ማብራሪያ ሰጥተዋል። የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶቹ በበኩላቸው በሚቀጥለው ዓመት የሚደረገውን 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ታሳቢ ያደረገ እቅድ ነድፈው የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን በተጠናከረ መልኩ ለመስጠት ዝግጅት እንደሚያደርጉ የገለጹ ሲሆን የተማሪዎች ተወካዮች በበኩላቸው ትምህርቱን በየትምህርት ቤታቸው በሚገኙ ሚኒ ሚድያዎችና በየወቅቱ በሚደረጉ ሁነቶች ለተማሪዎች ለማሰራጨት ማቀዳቸውን ገልጸው ቦርዱ ክትትልና ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል። የቦርዱ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ እና የስነ ዜጋና መራጮች ትምህርት የስራ ክፍል ባለሙያ ትምህርቱን በዘላቂ