ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የምርጫ ተሳትፎ እንዲጎለብት እየሠራ ነው
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁሉም የሀገራችን ዜጎች የፓለቲካ ተሳትፎ መብታቸው በተለይም የመመረጥና መምረጥ መብታቸው እንዲጎለብት አካታች የምርጫ ሥርዓትን ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።
ይህንንም ዕውን ለማድረግ ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በምርጫ ሂደት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያላቸውን ፍላጎት እና የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች በዳሰሳ ጥናት በመለየት ምቹ የምርጫ ከባቢ ለመፍጠር ኢስት አፍሪካ ከተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በአማካሪ ድርጅትነት ቀጥሮ በማስጠናት ላይ ይገኛል።
በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለታቀደው የዳሰሳ ጥናት አማካሪ ድርጅቱ የጥናቱን መነሻ ዕቅድ ሪፖርት ለቦርዱ ሥራ አመራር፣ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ዕቅዱን (Inception plan) የሚያጎለብቱ የሀሳብ ግብዓቶችን (ምክረ ሃሳቦችን) ሰብስቧል።