Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሴት ፓለቲካ ፓርቲ እና የግል ተወዳዳሪ ዕጩዎችን ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ነፃ፣ ገለልተኛ፣ ተዓማኒና ሁሉን አካታች ለማድረግ የሚያስችለውን በርካታ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። በዚኽም አግባብ ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ላይ ለሚወዳደሩ ሴት ፓለቲካ ፓርቲ እና የግል ዕጩዎች ሥልጠና ሰጥቷል።

ከሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ምርጫ በሚደረግባቸው በ13 ክልሎችና በሁለቱ ከተማ መስተዳድሮች በሚገኙ በ17 ከተሞች በተሰጠው ሥልጠና ላይ ከ1,731 በላይ ሴት ዕጩዎች የተሣተፉ ሲሆን፤ ዐላማውም ሴት ዕጩዎች በምርጫ ወቅት ሊያጋጥሟቸው የሚችሉ ፆታዊ ጥቃቶች መገለጫቸውና ምላሽ ስለሚሰጡበት ሕጋዊ አግባብ እንዲሁም የምርጫ ቅስቀሳ ላይ በሚኖራቸው ተሣትፎና የዐደባባይ ላይ ንግግሮችን ሲያደርጉ ሊከተሏቸው ስለሚገቡ ሥነ-ዘዴዎች ግንዛቤ እንዲያገኙ ማስቻል ነው።

Share this post

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሁናዊ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎቻቸውን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሁናዊ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎቻቸውን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋር ተወያየ። የውይይቱን መክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም የስብሰባው ዋና ዐላማ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እያደረጉ ባሉት ዝግጅት ላይ ያጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ለመወያየትና የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲሁም ለድምፅ መስጫው ቀን በቀሩት ጥቂት ቀናት ከማን ምን ይጠበቃል በሚለው ላይ ለመወያየት መሆኑን ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ትምህርት እንዲሰጡ ፍቃድ የሰጣቸው የሲቪል ማኅበረስብ ድርጅቶች ለተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የመራጮች ትምህርት ሰጡ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የመራጮች ትምህርት እንዲሰጡ የማሰተማሪያ ፍቃድ የሰጣቸው የሲቪል ማኅበረስብ ድርጅትች በደቡብ ኢትዮጵያ፣ በኦሮሚያ፣ በአማራ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በጋምቤላ፣ በሐረሪ፣ በአፋር፣ በሶማሌ፣ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ፣ በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ እና በሲዳማ ክልሎች እንዲሁም በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተማ መስተዳድሮች ለሚገኙ የተለያዩ የማኅበረሰብ ክፍሎች የመራጮች ትምህርት ሰጡ::

Share this post

ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለመወዳደር ለተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችን ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በግል ዕጩነት ለመወዳደር የተመዘገቡ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎችን አወያይ። አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት የተገኙበትን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ሲሆን፤ በንግግራቸውም፤ ቦርዱ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በጊዜ ሠሌዳው መሠረት ለማካሄድ ልዩ ልዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ መሆንኑ አስታውሰው፤ የግል ዕጩ ተወዳዳሪዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድልም የዚኹ አካል መሆኑን ተናግረዋል። የውይይቱ አንዱ አጀንዳ የሆነው የነፃ የዓየር ሰዓት ድልድልን አስመልክቶ ሲናገሩም የግል ዕጩዎቹ በሚያደርጉት የምረጡኝ ቅስቀሳ ወቅት ሕጉን ተከትለው በኃላፊነት ስሜት መሆን እንዳለበትና ይኽም የምርጫውን ሰላማዊ፣ ፍትሐዊና ተዓማኒነት በማረጋገጥ ረገድ ትልቅ ድርሻ እንዳለው ተናግረዋል።

Share this post

ቦርዱ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን የሚከታተል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት መጋቢት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ የሚካሄድባቸው አካባቢዎች የፀጥታ ሁኔታን የሚከታተል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራትን በተመለከተ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ። የውይይቱን የመክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ቀደም ሲል ከመንግሥት የፀጥታ ተቋማ በመቀጠልም ከፖለቲካ ፓርቲዎች የተሰበሰበውን የፀጥታ ሁኔታ መረጃ መሠረት አድርጎ የተለያዩ ውይይቶችን ማካሄዱን አስታውሰው፤ የዚኽም ውይይት ዋና ዐላማ ቀደም ሲል የቀረቡ መረጃዎች መሬት ላይ ወርዶ በትክክል ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ በመመልከት ሁኔታውን የሚመለከት የክትትል ቡድንን ሥምሪትና ተግባራት ላይ መወያየት በማስፈለጉ እንደሆነ ተናግረዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ መጋቢት 19 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ የዓየር ሰዓት ድልድል የዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት አካሄደ። የመድረኩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ በንግግራቸው ነፃ ዓየር ሰዓት ድልድሉን በዐዋጁ መሠረት ቦርዱ ከመገናኛ ብዙ`ኃን ባለሥልጣን ጋር በመሆን ለሣምንታት ሲያስተባብር እንደነበር ገልጸው፤ የሰዓት ድልድሉ ፖለቲካ ፓርቲዎች ፕሮግራማቸውንና ፖሊሲዎቻቸውን እንዲያስተዋውቁ፣ የግል ዕጩዎችም አማራጭ ሀሳባቻቸውን እንዲያጋሩና የምርጫ ቅስቀሳ እንዲያደርጉ፣ ከመራጩ ጋር እንዲተዋወቁ ዕድል የሚሰጣቸው መሆኑን ተናግዋል። ይፋ የተደረገው ነፃ የዓየር ሰዓትን የተመዘገቡ 46 ፖለቲካ ፓርቲዎችና የግል ዕጩዎች በኃላፊነት ስሜት እንዲጠቀሙበት በአፅንዖት አሳስበዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲዎች የክርክር መድረክ ማካሄድ ጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሚወዳደሩ ፖለቲካ ፓርቲዎች ያዘጋጀው የክርክር መድረክ የቦርዱን ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በይፋ ተጀመረ። መድረኩን በንግግር የከፈቱት ሜላትወርቅ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ይኽን የክርክር መድረክ ሲያዘጋጅ ፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃ፣ ገለልተኛና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ ፖሊሲዎቻቸውንና ፕሮግራሞቻቸውን የሚያስተዋውቁበት መድረክን መፍጠር ብቻ ሣይሆን፤ መራጩም በዛው ልክ አማራጭ የፖሊሲ ሃሳቦችን የመስማት ዕድል ኖሮት እንዲወሥን ለማስቻል በማሰብ መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ይኽ የክርክር መድረክ በመካሄድ ላይ ያለው የመራጮች ምዝገባ ላይ የበለጠ መነቃቃትን እንደሚፈጥር ተናግረው፤ መራጮችም በማንዋልና በዲጂታል አማራጭ በመካሄድ ላይ ያለው የመራጮች ምዝገባ ከመጠናቀቁ በፊት ተመዝግበው ካርድ እንዲወስዱ አስታውሰዋል።

Share this post

ቦርዱ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖራቸውን ቅደም ተከተል ለመወሠን የሚያስችለውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የፖለቲካ ፓርቲ ዕጩዎች በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖራቸውን ቅደም ተከተል ለመወሠን የሚያስችለውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ዛሬ መጋቢት 14 ቀን 2018 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በትላንትናው ዕለት መጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም. 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ የሚደረግባቸው አካባቢዎችን የፀጥታ ሁኔታ በተመለከተ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ። የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉን ጨምሮ አምስቱም የቦርድ ሥራ አመራር አባላት በተገኙበት በተደረገው ውይይት ላይ ቦርዱ ቀደም ሲል ከፖለቲካ ፓርቲዎች የሰበሰበው ሥጋት አለባቸው ብለው የለዩዋቸው አካባቢዎች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፤ በውይይቱ ከተነሡ ተጨማሪ አጀንዳዎች ውስጥም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ያለ የፀጥታ ሥጋትና በነፃነት የምረጡኝ ቅስቀሳ ያማድረግ ሁኔታ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ያለምንም ተፅዕኖ ሥራቸውን ማከናወን፣ የፖለቲካ ምኅዳርን በተመለከተ የተቸገሩ መሆኑ ይጠቀሳሉ።

Share this post

ስለ ዲጂታል መራጮች ምዝገባ የተሰጠ ማብራሪያ

የመጪውን ምርጫ ግልጽ፣ ተዓማኒ እና ቀልጣፋ ለማድረግ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን ማሳደግ አንዱ የሪፎርም አካል መሆኑ ይታወቃል።

በዚህም መሠረት የዲጂታል መራጮች ምዝገባ ሥርዓትን በሥራ ላይ ለማዋል ዝግጅቶች ተጠናቀው ወደ ተግባር ተገብቷል። ይሁን እንጂ፣ በዛሬው ዕለት የተጀመረው የዲጂታል መራጮች ምዝገባ በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች ሳይሆን በተመረጡ ጣቢያዎች ላይ ብቻ የሚከናወን መሆኑን በድጋሚ ለሕዝብ ግልጽ ማድረግ እንወዳለን።

መራጮች ሊገነዘቧቸው የሚገቡ ዋና ዋና ነጥቦች፦

የዲጂታል ምዝገባው የሚካሄደው አስቀድመው ለዚህ ተግባር በተለዩ ውስን ጣቢያዎች ብቻ ነው።

በዲጂታል ምዝገባ በማይካሄድባቸው ሌሎች ጣቢያዎች ሁሉ፣ የመራጮች ምዝገባ እንደተለመደው በመዝገብ (በማኑዋል) የሚቀጥል ይሆናል።

Share this post