Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የሚያስፈጽመውን የ6ኛው ዙር ቀሪና እና የድጋሚ ምርጫን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር፣ በሶማሌ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. የ6ኛው ዙር ቀሪና እና የድጋሚ ምርጫ ድምፅ የመስጠት ሂደትን እንደሚያስፈጽም ይታወቃል። በዚህም መሠረት በዕለቱ የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ ድምፃቸውን መስጠት እንዲችሉ፤ እንዲሁም የድምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወን ለማስቻል፤ ቦርዱ የሚከተሉትን ተግባራት ተፈጻሚ እንዲሆኑ “የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የሥነ‐ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161” ላይ በተደነገገው የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊና መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ከታች የተዘረዘሩትን ተግባራት ያሳውቃል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚያደርገውን የ6 ኛው ዙር ቀሪና የድጋሚ ምርጫን ለመዘገብ ከቦርዱ እውቅና ላገኙ የመገናኛ ብዙኃን ሰኔ 12 ቀን 2016 ዓ.ም. ሥልጠና ሠጠ፡፡

ስልጠናው የመገናኛ ብዙኃን እና የጋዜጠኞች የምርጫ አዘጋገብ ስነ ምግባርን ላይ አትኩሮት አድርጎ የምርጫ ዑደትና የምርጫ ሕግ ማዕቀፍን፤ ምርጫውን የተመለከቱ አጠቃላይ መረጃዎችን፤ አካታች የምርጫ ዘገባ ባህሪያትን እና የተዛቡ፤አሳሳች፤አደናጋሪና በአጋጣሚ ወይም ሆን ተብለው የሚፈጠሩ የመረጃ መዛባቶችን እና የመረጃዎችን ትክክለኛነት ለመፈተሽ በሚያስችሉ የዲጂታል እውቀቶች እና አጠቃቀሞች ዙሪያ ያተኮረ ነበር፡፡

Share this post

ስለ ጥሞና ወቅት መረጃዎች

የጥሞና ወቅት በቅድመ የምርጫ ዑደት ውስጥ የሚገኝ ጊዜ ሲሆን፤ በኢትዮጵያ የምርጫ ዑደት መመሪያ መሠረት ምርጫ ከመደረጉ በፊት ያሉትን አራት ቀናት ያካትታል፡፡ በጥሞና ወቅት ታዲያ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት፤ ማለትም የፖለቲካ ፓርቲዎች፣ የመገናኛ ብዙኃን ተቋማት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ኃላፊነቶች አሉ፡፡

የፖለቲካ ፓርቲዎች

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ ማስተዋወቂያ መድረክ አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ነፃ፣ ፍትሃዊ እና ተዓማኒነት ባላቸው ምርጫዎች እና የህዝብ ውሳኔዎች አማካይነት በኢትዮጵያ ዲሞክራሲን ማጎልበትንና ማፅናትን ዋና ስትራቴጂያዊ ግቡ ያደረገ ከ2016/17 ዓ.ም እስከ -2020/21 ዓ.ም የሚተገበር ስትራቴጂክ ዕቅድ ይፋ አደረገ።

ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚተገበረው የስትራቴጂክ ዕቅድ ስድስት አምዶችን (pillars) ማለትም የምርጫ ሕግ ማዕቀፍ፣ የዜጎች ተሳትፎና የግብ ትስስር፣ የምርጫ ሥራዎች፣ የምርጫ ባለድርሻ አካላት ተሳትፎና አጋርነት፣ ተቋማዊ ለውጥና ግንባታ እንዲሁም የምርጫ ቴክኖሎጂ እና ፈጠራን ማእከል አድርጎ የተዘጋጀ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ዉጤቶችን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መሀከል መራጮች በቂ የምርጫ ነክ መረጃ እና ግንዛቤ የሚያገኙበትን አካታች ስልት መቀየስ እና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን መስጠት አንዱ ነዉ፡፡ በዚህም መሰረት የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን ለአካል ጉዳተኛ ማህበረሰቦች በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ በስፋት እየሠራ ይገኛል፡፡ይህንን ተከትሎ ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም የተለያዩ በብሬል የተዘጋጁ የህትመት ዉጤቶችን፣ ማለትም ምርጫ በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ የተዘጋጂ ቡክሌቶች፣ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አዋጆችን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኬኔዲ እና ሕግ ላይብረሪ ክፍል አስረክቧል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 2016 ዓ.ም. በሚያካሂደው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ለሚወዳደሩ ሴት ዕጩ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት እንዲሁም ለታዛቢ ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች እና የሰብአዊ መብት ተከታታዮች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 16 ቀን 2016 ዓ.ም.

Share this post

የዕጩዎችን ዝርዝር ይፋ ስለማድረግ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ በሚካሄድባቸው ቤንሻንጉል ጉሙዝ ፣አፋር ሶማሌ እና መስቃን እና ማረቆ-2 የምርጫ ክልሎች ላይ የእጩዎች ምዝገባ ከሚያዝያ 21 አስከ ግንቦት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. ማከናወኑ ይታወቃል። በመሆኑም የምርጫ ሕጉ ተወዳዳሪ እጩዎችን ቦርዱ ለህዝብ ይፋ እንዲያደርግ በደነገገው መሰረት ቦርዱ በቦርዱ የተረጋገጡ የእጩዎችን ዝርዝር ከዚህ በታች ይፋ አድርጓል፡፡

 PDFለተወካዮች ምክር ቤት የሚወዳደሩ ዕጩዎች ዝርዝር

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 2016 ዓ.ም. በሚያካሂደው ምርጫ የሚወዳደሩ ዕጩዎች በድምፅ መስጫ ወረቀት ላይ የሚኖራቸውን ቅደም ተከተል የሚወሥነውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት አካሄደ ::

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሚያካሂደው ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚህም ተግባራት አንዱ የዕጩዎች ምዝገባ ሲሆን፤ በትላንትናው ዕለት ማለትም ግንቦት 13 ቀን 2016 ዓ.ም. የተመዘገቡ ዕጩዎችን በድምፅ መስጫ ወረቀቱ ላይ የሚኖራቸውን የአደራደር ቅደም ተከተል የሚወሥነውን የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት አካሂዷል።

በዚህ የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት ላይ የቦርዱ ዋና ሰብሳቢን ጨምሮ ሁሉም የቦርድ አመራር አባላትና በምርጫው ላይ የሚሣተፉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዩች የተገኙ ሲሆን፤ ሥነ-ሥርዓቱም የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ተከፍቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የቦርድ አመራር አባላት ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ምርጫ በሚካሄድባቸው አካባቢዎች የምርጫ ሥራዎችን በተመለከተ የመስክ ምልከታና ከባለድርሻ አካላት ጋር ለሁለት ቀናት የቆየ ምክክር አካሄዱ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የአፋር፣ የሶማሌ እና የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ለሚያካሂደው ምርጫ የተለያዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ይህንንም ተከትሎ የመራጮች ምዝገባ ከሚያዚያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በመከናወን ላይ በሚገኝባቸው በቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ በአፋር እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች የቦርዱ የበላይ ኃላፊዎች የመሥክ ጉብኝት እና ውይይት ከግንቦት 7-8 ቀን 2016 ዓ.ም. አካሂደዋል፡፡

በመስክ ጉብኝቱ በምርጫ ክልሎቹ ላይ እየተከናወነ ያለውን የምርጫ ነክ ሥራዎች ምን እንደሚመስሉ ከመመልከታቸው በተጨማሪ፤ በምርጫ ጣቢያዎቹ በመከናወን ላይ ያለውን የመራጮች ምዝገባ አጠቃላይ ሁነትን የተመለከቱ ሲሆን በየምርጫ ጣቢያዎቹ በሥራ ላይ ከነበሩ ከመራጮች ምዝገባ አስፈጻሚዎች ጋር ውይይት ተደርጓል።

Share this post

NEBE study visit in Berlin

The Board of NEBE was invited to Germany by its long-standing partner: the Netherlands Institute for Multiparty Democracy (NIMD). The study visit was in Berlin from the 15th to the 19th of April 2024.

The study visit focused on: Germany's electoral system (legal framework, institutions and management); learning about political party registration, administration/regulation; and getting an understanding of the Berlin State Election Commission's relations with other Governmental organs (Federal Parliament and Regional Parliaments)

Share this post