Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4/12 ምክር ቤት ጋር በመተባበር በዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታና በምርጫ ሂደት ዙሪያ ሥልጠና ሰጠ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4/12 ምክር ቤት በተደረገለት ግብዣ መሰረት የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት ክፍል ከቦርዱ አዲስ አበባ ቅ/ጽ/ቤት እንዲሁም ከምርጫ ኦፐሬሽንስ የሥራ ክፍል ጋር በመቀናጀት ለሕፃናት ፓርላማ አባላትና ለባለድርሻ አካላት በዲሞክራሲያዊ ምርጫ የዜጎች መብትና ሃላፊነቶች፥ የኢትዮጵያ የምርጫ ሂደትን ከምርጫ ህጉ አኳያ እና በሕፃናት የፓርላማ አሰራር፥ አወቃቀርና መልሶ ማደራጀት ዙሪያ ላይ ያተኮረ የአንድ ቀን ሥልጠና የካቲት 16 ቀን 2016 ዓ.ም. ሰጥቷል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ኮንግረስ ፓርቲ ከሀገር ዓቀፍ የፖለቲካ ፓርቲነት እንዲሰረዝ የኢትጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የወሰነውን ውሳኔ የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በመቀበል የሰጠው ውሳኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ አንድነት ኮንግረስ በአዋጅ ቁጥር 1162/11 መሰረት በሀገር ዓቀፍ ፓርቲነት ለመመዝገብ ጥያቄ አቅርቦ በአዋጁ አንቀጽ 64 መሰረት ፓርቲው ከአምስት ክልሎች ማቅረብ የሚገባውን አስር ሺህ (10,000) የመስራች አባላት በቁጥር ያቀረበ ቢሆንም የክልላዊ አባላት ስብጥርን በሚመለከት ግን ከአንድ ክልል መሟላት ከሚገባው አንድ ሺህ አምስት መቶ (1,500) መስራች አባላት ውስጥ አንድ ሺህ አርባ አምስት (1,045) መስራች አባላት ብቻ ያቀረበ በመሆኑ ለሀገር ዓቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ የሚያስፈልገውን የመስራች አባላት ክልላዊ ስብጥር አሟልቶ ስላልቀረበ ከየካቲት 29 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ከፖለቲካ ፓርቲነት እንዲሰረዝ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ወስኖ ነበር፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በስነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት ላይ በትኩረት እየሠራ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ላይ በትኩረት እየሠራ ሲሆን ዜጎች በቂ የስነ-ዜጋ እና ምርጫ ነክ ግንዛቤ እንዲኖራቸው ቦርዱ የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም ትምህርት እየሰጠ ይገኛል። በዚሁ መሠረት የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል ከቦርዱ የአዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ጋር በመቀናጀት በቅርቡ በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ ትምህርት ቤቶች እና የህዝብ ቤተ-መጻሕፍት አስተማሪ የሆኑ የተለያዩ የሕትመት ውጤቶችን ማለትም ቡክሌት እና ብሮሸሮችን የግንዛቤ ገለፃ በመስጠት ማሰራጨት ተችሏል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ለሚሰጡ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ስልጠና እና የእውቅና ምስክር ወረቀት ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርት የሥራ ክፍል በምርጫና ተያያዥ ጉዳዮች ዙሪያ ከሚሠሩ 40 የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጋር ከ ጥር 29 እስከ ጥር 30 ቀን 2016ዓ.ም. ድረስ ለሁለት ቀናት የቆየ የስልጠና መድረክ አዘጋጀ። መድረኩ በምርጫ ቦርድ አመራር አባል ዶ/ር አበራ ደገፋ የመክፈቻ ንግግር የተከፈተ ሲሆን በመክፈቻ ንግግራቸው የስነ-ዜጋና መራጮች ትምህርትን በቋሚነት የመስጠትን ጠቀሜታ ካብራሩ በኋላ ይህ እንዲሳካ ከቦርዱ ባልተናነሰ የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማት ዋነኛ ሚና እንደሚጫወቱ አብራርተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዓ.ም. በተሰጠው ሥልጣን መሠረት፣ ለሶስት የፖለቲካ ፓርቲዎች የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በኢትዮጵያ የምርጫ፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 ዓ.ም. በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ‘የወሎ ህዝቦች ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ’ ተብሎ ለሚጠራ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ፤‘የኩሽ ህዝቦች ብሔራዊ ንቅናቄ’ ተብሎ ለሚጠራ ክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ እና ‘ብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ’ ለተባለ ሀገር አቀፍ የፖለቲካ ፓርቲ ጥር 21 ቀን፣ 2016 ዓ.ም የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ሰጠ፡፡

Share this post

የጨረታ ማስታዎቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛውን አጠቃላይ ምርጫ ተከትሎ የአካል ጉዳተኞችን ተሳትፎ እና የምርጫ ጣቢያዎችን ተደራሽነት የሚፈትሽ የዳሰሳ ጥናት እንዲሰሩ አማካሪ ድርጅቶችን አወዳድሮ ለመቅጠር ይፈልጋል ስለሆነም በዘርፉ የተሰማራችሁ አማካሪ ድርጅቶች እና ባለሞያዎች እስከ ጥር 27 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ በምርጫ ቦርድ ዋናው ቢሮ ግዢ ክፍል ቢሮ ቁጥር 107 በመምጣት የጨረታ ሰነዳችሁን ማስገባት ትችላላችሁ፡፡

ስለሥራው ዝርዝር መረጃ ከስር ያለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ማግኘት ትችላላችሁ፡፡

እዚህ ላይ ይጫኑ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከ UNDP (United Nations Development Programme)ጋር በመተባበር በ BRIDGE (Building Resources in Democracy, Governance and Elections) አማካሪዎች አማካኝነት ለምርጫ ቦርድ የበላይ አመራሮች እና ኃላፊዎች ሥልጠና ሰጠ

ሥልጠናው “የምርጫ ተቋማዊ ልህቀት ግንባታ” (Building Institutional Excellence in Elections) በሚል ርዕስ የተሰጠ ሲሆን የቦርድ አባላት፤ የጽ/ቤት ኃላፊዎች፤ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች እና ከቦርዱ የክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የተውጣጡ በድምሩ 25 የሚሆኑ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈውበታል፡፡

ሥልጠናው በዋናነት የምርጫ አስተዳደርን፣ መዋቅራዊ አደረጃጀትን፣ ዕቅድን፤ የድርጅት ባህልን፤የውስጥ እና የውጭ ተግባቦትን፤አጋርነትን እና ስኬታማ የአመራር ሂደትን በተመለከቱ ሃሳቦችን ዙሪያ ያተኮረ ነበር፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት ኤጄንሲ አብረው ለመሥራት የሚያስችላቸው የመግባቢያ ሠነድ ተፈራረሙ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መራጮች በቂ የሆነ የሥነ-ዜጋ እና የምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ስልት በመቀየስና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት ከዋና ዋና ተግባራቱ መካከል አንዱ ነው፡፡ ቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ ይረዳው ዘንድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣ በህዝብ ቤተ-መጻሕፍት፣ በመንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ በማድረግ ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየሠጠ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቦርዱ የዕቅድ ዝግጅት፣ ክትትል እና ግምገማ የሥራ ክፍል አስተባባሪነት 45 ለሚሆኑ የቦርዱ የክልል ጽ/ቤት ኃላፊዎች፣ የዲፓርትመንት ኃላፊዎች እና ኤክስፐርቶች በዕቅድ ዝግጅት (Planning)፣በጀት አያያዝ (Budgeting)፣ ክትትል እና ግምገማ (Monitoring and Evaluation)፣ የአፈጻጸም ሪፖርት አዘገጃጀት (Reporting)፤የሠራተኛ ምዘና (Performance Evaluation and Coach for Performance) ላይ ያተኮረ ሥልጠና እየሠጠ ይገኛል፡፡

ከታህሣሥ 22 እስከ ታህሣሥ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ የሚቆየው ሥልጠና ዋና ዓላማ እያንዳንዱ ኃላፊ የሥራ ክፍሉን ተግባራት ለማቀድ፤በጀት ለመመደብ እና ደረጃውን የጠበቀ ሪፖርት ለማቅረብ የሚያስችለውን ዕዉቀት እና ክህሎት ለማስጨበጥ ያለመ ነው፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የሕትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣በህዝብ ቤተ- መጻሕፍት፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ እያደረገ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መሀከል መራጮች በቂ የምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ስልት መቀየስና በተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎች በመጠቀም የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርትን መስጠት አንዱ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርትን በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ የተለያዩ የሕትመት ውጤቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣በህዝብ ቤተ- መጻሕፍት፣ መንግሥታዊ እና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ እያደረገ ይገኛል።

Share this post