ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሁናዊ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎቻቸውን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ተወያየ
ቦርዱ በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አሁናዊ ሂደት ላይ እያጋጠሙ ያሉ ተግዳሮቶችንና መፍትሔዎቻቸውን አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ግንቦት 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ጋር ተወያየ። የውይይቱን መክፈቻ ንግግር የቦርዱ ሰብሳቢ ሜላትወርቅ ኃይሉ ያደረጉ ሲሆን፤ በንግግራቸውም የስብሰባው ዋና ዐላማ ፖለቲካ ፓርቲዎቹ ለ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ እያደረጉ ባሉት ዝግጅት ላይ ያጋጠሟቸው ተግዳሮቶች ላይ ለመወያየትና የመፍትሔ አቅጣጫ ለማስቀመጥ እንዲሁም ለድምፅ መስጫው ቀን በቀሩት ጥቂት ቀናት ከማን ምን ይጠበቃል በሚለው ላይ ለመወያየት መሆኑን ተናግረዋል።