የኢትዮጽያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥራ ላይ ያለው ሕግን ማሻሻል የተመለከተ ዐውደ-ጥናት አካሄደ
የኢትዮጽያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዛሬ ታኅሣሥ 7 ቀን 2017 ዓ.ም. በሥራ ላይ ያለው “የኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011” የተመለከተ የሕግ ማሻሻያ ዐውደ ጥናት አካሄደ።
አምስቱም የቦርድ አመራር አባላት፣ የየሥራ ክፍል ኃላፊዎችና ከፍተኛ ባለሞያዎች እንዲሁም የቦርዱ የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች የተገኙበትን ዐውደ-ጥናት በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ሰብሳቢ የሆኑት ሜላትወርቅ ኃይሉ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ስድስተኛው ሀገር ዐቀፍ ምርጫን ተከትሎ ከባለድርሻ አካላት ጋር በተካሄዱ የድኅረ-ምርጫ መልካም ተሞክሮዎችና ተግዳሮቶች ግምገማ መድረክ ላይ የተነሡትን የሕግ ማሻሻያ የሚፈልጉ ዐዋጁ ላይ ያሉ ድንጋጌዎች ፤ ከሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ ቀደም ብሎ በመለየት፤ ዓለም ዐቀፍ መመዘኛዎችን ባማከለና የተሻለ አፈጻጸምና ግልጸኝነትን ለማጎልበት እንዲረዳ ተደርጎ ማሻሻያ እንደተደረገበት ተናግረዋል።