Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለሙያዎች ዘመናዊ የሪከርድና መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችላቸውን ስልጠና ወሰዱ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች በዶክመንቴሽን፣ በሪከርድ እና መረጃ አስተዳደር ርዕሰ ጊዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች አማካኝነት ከ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ የቆየ ስልጠና ተሰጥቷል።

አስር ቀን በቆየው ስልጠና በቦርዱ የሥራ ሂደት የሚሰበሰቡ ሪከርዶች ታሪካዊ ፋይዳቸው የላቀ በመሆኑ ሳይንሳዊ በሆነ ዘመናዊ የሪከርዶች አስተዳደር ስርዓት መደራጀት እና መጠበቅ እንዳለባቸው አፅንዖት ተሰጥቶታል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥነ-ዜጋ ትምህርት እና በምርጫ ዙሪያ የተዘጋጁ የኅትመት ውጤቶችን በሕዝብ ቤተ-መጻሕፍትና በተለያዩ ተቋማት የማሠራጨት ሥራ አከናወነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በቦርዱ ማቋቋሚያ ዐዋጅ 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር የሥነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት እንደሚሰጥ እና እንደሚያስተባብር ይታወቃል። ይህውም መራጮች በቂ ምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙባቸውን የተለያዩ አማራጮች በመጠቀም ማለትም በኅትመት ውጤቶች (በበራሪ ወረቀቶች፣ በቡክሌት፣ በብሮሸሮች እና በሌሎች አማራጮች) ግንዛቤ የሚፈጥሩ መልዕክቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣ በቤተ-መጻሕፍት እንዲሁም በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ የማድረግ ሥራ ይሠራል። ቦርዱ ከላይ የተጠቀሰውን ኃላፊነት ለመወጣት በቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ክፍል አማካኝነት የግንዛቤ መስጫ ኅትመቶቹን በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬልም ጭምር እያዘጋጀ በማሠራጨት ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በወላይታ ዞን ሲያከናወን የቆየዉን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ውጤት የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርጓል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በ1,812 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያስፈጸመውንና 849,896 መራጮች ድምፅ የሰጡበትን የወላይታ ዞን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የውጤት ማዳመሩን ሥራ በዞኑ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሲያከናወን መቆየቱ ይታወቃል። በዛሬውም ዕለት ቦርዱ የውጤት የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።

ዝርዝር መግለጫዉን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በዎላይታ ዞን ለሚያስፈጽመው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ወደ ዎላይታ ዞን የማጓጓዝ ሥራ ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሁለት ቀናት በኋላ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በዎላይታ ዞን ለሚያስፈጽመው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚህም የቅድመ ምርጫ ተግባራት ውስጥ አንዱ ከአዲስ አበባ በመመልመል ያሠለጠናቸውን የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች ከአዲስ አበባ የሕዝበ ውሣኔው ወደ’ሚካሄድበት ዎላይታ ዞን ውስጥ ወደ’ሚገኙ 1,804 ምርጫ ጣቢያዎች በሁለት ዙር ማጓጓዝ ይጠቀሳል። በዚህም ሰኔ 6 እና ሰኔ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. በድምሩ 5215 አስፈጻሚዎች ወደ ዎላይታ ዞን የማጓጓዝ ሥራው ተጠናቋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በወላይታ ዞን ለሚያስፈጽመው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በወላይታ ዞን ለሚያስፈጽመው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ ይገኛል። ከነዚህም ተግባራት ውስጥ አንዱ ከአዲስ አበባ ተመልምለው ስልጠና የወሰዱ የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎችን ከአዲስ አበባ ወደ ሕዝበ ውሣኔው የሚካሄድበት ወላይታ ዞን ውስጥ ወደሚገኙ 1,804 ምርጫ ጣቢያዎች ማጓጓዝ ይጠቀሳል። ይህንንም ተግባር በትላንትናው ዕለት ሰኔ 5 ቀን 2015 ዓ.ም የተጀመረ ሲሆን፤ በመጀመሪያው ዙር 2,495 አስፈጻሚዎች መነሻውን ከሚሊንየም አዳራሽ አድርጎ በዞኑ ወደተመደቡበት የምርጫ ጣቢያዎች የማጓጓዝ ሂደት በዛሬው ዕለት ሰኔ 6 ቀን 2015 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት በሶዶ ከተማ ሁሉም ተገኝተው ወደ ማዕከሎቻቸው ተጉዘው ከፊሎቹ ደርሰዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን ለሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም በወላይታ ዞን የሚያካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ላይ ለሚሣተፉ በየደረጃው ለሚገኙ የምርጫ አስፈጻሚዎች ሥልጠና ሰጠ። ከግንቦት 16 ቀን እስከ ግንቦት 21 ቀን 2015 ዓ.ም በተሰጠው ሥልጠናም የሥራ ትውውቅ፣ የውጤት ማመሳከር፣ የማዳመርና የይፋ አደራረግ ላይ ያተኮረ ሥልጠና ለዞንና ለማዕከል አስተባባሪዎች የተሰጠ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞችም እንዲሁ የአሠልጣኞች ሥልጠና በሶዶ ከተማ ተሰጥቷል።

በተጨማሪም ቦርዱ በወላይታ ዞን ውስጥ በተቋቋሙ 12 ማስተባበሪያ ማዕከላት ላይ ለ3608 የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች በሁለት ዙር ሥልጠና በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ የመጀመሪያው ዙር ሥልጠና ከግንቦት 23 እስከ ግንቦት 25 ቀን 2015 ዓ.ም ሲሰጥ፤ የሁለተኛ ዙር ሥልጠናም እንዲሁ ከግንቦት 26 እስከ ግንቦት 28 ቀን 2015 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን በሚካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ የመራጮች ትምህርት ላይ ከሚሣተፉ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ውይይት አካሄደ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን በሚካሄደው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔን ምርጫ ላይ የመራጮች ትምህርት ተደራሽነት ላይ ለሚሠሩና በቦርዱ የገንዘብ ድጋፍ ከተደረገላቸው ሰባት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ጋር ግንቦት 23 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። ዐላማውን ድጋፍ የሚደረግላቸው ድርጅቶች የሚደረግላቸውን ድጋፍ በምን አግባብ መጠቀም እንዳለባቸው፤ እንዲሁም ከዕቅድ አንጻር አፈጻጸማቸውና የፋይናንስ ሪፖርት አቀራረባቸውን አስመልክቶ ግልጽ መግባባት ላይ ለመድረስ ያደረገውን ውይይት በንግግር የከፈቱት የቦርድ አመራር አባል የሆኑት ዶ/ር አበራ ደገፋ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም ቦርዱ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም.

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ላይ ያስተላለፈውን የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ፓርቲው ይነሣልኝ ሲል ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ ውድቅ ያደረገበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ሲል በሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ሕ.ወ.ሓ.ት) ላይ ያስተላለፈውን የፓርቲውን ሕጋዊ ሰውነት ሥረዛ ፓርቲው ይነሣልኝ ሲል ያቀረበውን ጥያቄ ቦርዱ ውድቅ ያደረገበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፓርቲው አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የብሔራዊ ባይቶ ዓባይ ትግራይ (ባይቶና) ፓርቲው አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የሳልሳይ ወያነ ትግራይ ፓርቲ አደራጅ ኮሚቴ ዐዋጁን መሠረት በማድረግ የመሥራች ጉባዔውን እንዲያከናውን መወሠኑን ያሳወቀበት ደብዳቤ ለማግኘት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post