የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በመነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት በተከናወነው የታላቁ ሩጫ ፕሮግራም ማስተዋወቂያ ላይ በመገኘት ለታዳጊ ተማሪዎች ስለምርጫ ምንነትና የድምጽ አሰጣጥ ሂደት በተግባር የተደገፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ አደረገ፡፡
የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ የሴቶች እና የአካል ጉዳተኞች ሩጫ አስተባባሪዎች የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድን ጨምሮ ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ለመነን የልጃገረዶች አዳሪ ትምህርት ቤት ፕሮግራሙን አስተዋውቋል፡፡ በዚህ መርሀ ግብር ላይ የተጋበዘው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለትምህርት ቤቱ ማህበረሰብ በተለይም ለታዳጊ ተማሪዎች ስለምርጫ ምንነት እና በኢትዮጵያ የምርጫ ሂደት ዙሪያ በተግባር የተደገፈ የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለፃ አድርጓል፡፡