የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የተፈፀሙ ዋና ተግባራት
የዕቅድና በጀት ዝግጅት
- ህዝበ ውሣኔውን የሚካሄድባቸውን ቦታዎች እና ምርጫ ጣቢያዎችን በመለየት፣ መረጃዎችን በማሰባሰብ እና በማደራጀት ቦርዱ ዝርዝር ዕቅድ አዘጋጅቶ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አቅርቧል። (መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም)
- የህዝበ ውሳኔውን ለማስፈጸም ከተጠየቀው በጀት ብር 541 ,270,104.82 (አምስት መቶ አርባ አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺ አንድ መቶ አራት ብር ከሰማኒያ ሁለት ሳንቲም) ውስጥ 410,100,000 (አራት መቶ አስር ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ) ተፈቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። (ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ/ም)
- በቀጣይም ተጨማሪ በጀት የሚያስፈልጋቸውን ዝርዝር ተግባራት አዘጋጅቶ ያቀርባል።
የህዝበ ውሳኔ ጽ/ቤቶችን ማደራጀት