Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ በነሐሴ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. አቶ አምሀ ዳኜው ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ያሣለፈውን ውሣኔና በተመለከተ የተሰጠ ማብራሪያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ብሔራዊ ምክር ቤት በነሐሴ 15 ቀን 2014 ዓ.ም. ለሦስተኛ ጊዜ ተጠርቶ አቶ አምሀ ዳኜው ምክትል ፕሬዚዳንት እንዲሆኑ ያሣለፈውን ውሣኔና ጠቅላላ ጉባዔ ለመጥራት የሄደበት ሂደት አስመልክቶ ፓርቲው ያቀረበውን ሠነድ ከዐዋጁና ከፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ አንጻር በመመርመር ሂደቱ የተሟላ በመሆኑ ቦርዱ ተቀብሎታል። በመሆኑም ፓርቲው ጠቅላላ ጉባዔውን የሚያካሂድበትን ቀን በመቁረጥ ለቦርዱ በማሳወቅ እንዲያከናውን ቦርዱ ወሥኗል።

ደብዳቤው እዚህ ላይ ያገኙታል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሂደው ሕዝበ ውሣኔ የተፈፀሙ ዋና ተግባራት

የዕቅድና በጀት ዝግጅት

  • ህዝበ ውሣኔውን የሚካሄድባቸውን ቦታዎች እና ምርጫ ጣቢያዎችን በመለየት፣ መረጃዎችን በማሰባሰብ እና በማደራጀት ቦርዱ ዝርዝር ዕቅድ አዘጋጅቶ ለህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አቅርቧል። (መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም)
  • የህዝበ ውሳኔውን ለማስፈጸም ከተጠየቀው በጀት ብር 541 ,270,104.82 (አምስት መቶ አርባ አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሺ አንድ መቶ አራት ብር ከሰማኒያ ሁለት ሳንቲም) ውስጥ 410,100,000 (አራት መቶ አስር ሚሊዮን አንድ መቶ ሺ) ተፈቅዶ ወደ ሥራ ተገብቷል። (ጥቅምት 1 ቀን 2015 ዓ/ም)
  • በቀጣይም ተጨማሪ በጀት የሚያስፈልጋቸውን ዝርዝር ተግባራት አዘጋጅቶ ያቀርባል።

የህዝበ ውሳኔ ጽ/ቤቶችን ማደራጀት

Share this post

የቡሌ ምርጫ ክልል የድጋሚ ምርጫን በተመለከተ የተሰጠ ውሣኔ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. እና መስከረም 20 ቀን 2014 ዓ.ም. በሁለት ዙር ማከናወኑ ይታወቃል። ቦርዱ በተያዘው በጀት ዓመት በተለያዩ ምክንያቶች 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ባልተካሄዱባቸው የተወሠኑ የምርጫ ክልሎች ላይ ምርጫ ለማከናወን የቅድመ ዝግጅቶች ሥራዎችን በማድረግ ላይ ይገኛል።

ቀደም ሲል ቦርዱ 6ኛውን ሀገራዊ ምርጫ ካካሄደባቸው ምርጫ ክልሎች አንዱ በሆነው በቡሌ ምርጫ ክልል የተካሄደው ሀገራዊ ምርጫ ላይ መጠነ ሰፊ የሕግ ጥሰት እንደነበር በማረጋገጡ ምርጫው በድጋሚ እንዲከናወን ጥቅምት 19 ቀን 2014 ዓ.ም. መወሠኑ ይታወቃል። ይህንንም የድጋሜ ምርጫ በተያዘው ዓመት በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ከሚካሄደው ሕዝበ ውሣኔ ጋር በአንድ መርኅ ግብር ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. አብሮ እንዲከናወን ቦርዱ ኅዳር 03 ቀን 2015 ዓ.ም. ወሥኗል።

Share this post

ማስታወቂያ: በምርጫ አስፈጻሚነት መሣተፍ ለሚፈልጉ አመልካቾች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደ/ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚያካሄደው ሕዝብ ውሣኔ፤ በምርጫ አስፈጻሚነት ለመሣተፍ ፍላጎት ያላቸውን አመልካቾች ማስታወቂያ በማውጣት መመዝገቡ ይታወቃል። ሆኖም ሕዝበ ውሣኔው በሚካሄድባቸው የተወሠኑ ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች ውስጥ ባሉ ቀበሌዎች እና ምርጫ ጣቢያዎች ላይ በቂ ምርጫ አስፈጻሚ ባለመገኘቱ ፍላጎት ያላቹ አመልካቾች እስከ ኅዳር 12 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ከታች የተቀመጠውን ማስፈንጠሪያ በመጫን እንድታመለክቱ ቦርዱ ያሳውቃል።

ለማመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ

ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ ዐዋጅ ቁጥር 1133/2011 እና በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር ዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 መሠረት የፖለቲካ ፓርቲዎችን የመመዝገብ ኃላፊነት ተሰጥቶታል።

በዚሁ መሠረት በእነአቶ ዩሱፍ ሁሴን “የሱማሌ ፌዴራሊስት ፓርቲ (ሱ.ፌ.ፓ)” በሚል ስያሜ የክልላዊ የፖለቲካ ፓርቲ የምዝገባ ጥያቄ ያቀረቡ በመሆኑ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 68 ንዑስ አንቀጽ ሁለት እና ሦስት መሠረት በፓርቲው ስም፣ ዐርማ ወይም ሌሎች ጉዳዮች ተቃውሞ ያለው ሰው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከዛሬ ኅዳር 8 ቀን 2015 ዓ. ም. ጀምሮ በ14 ቀናት ውስጥ ተቃውሞውን የቦርዱ ዋናው መሥሪያ ቤት 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁ. 207 እንዲያቀርብ ቦርዱ ያሳስባል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ማሳሰቢያ: በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ መዘገብ ለምትፈልጉ መገናኛ ብዙኃን አካላት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን አካላት ጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. የምዝገባ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫን ለመዘገብ ከቦርዱ የዕውቅና ባጅ ያገኙ የመገናኛ ብዙኃን አካላት፤ ሀገራዊ ምርጫውን ለመዘገብ የተሰጣቸው ባጅ ጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ በሚካሄደው ሕዝበ ውሣኔ ጥቅም ላይ መዋል የማይችልና አገልግሎቱ ያበቃ መሆኑን በመገንዘብ እንደገና ማመልከት እንደሚጠበቅባቸው ቦርዱ ያሳውቃል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ላይ ለሚካሄደው ሕዝበ ውሣኔ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ለመስጠት በቦርዱ ፈቃድ የተሰጣቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዐዋጅ ቁጥር 1162/2011 አንቀጽ 124 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት መራጮች በቂ ምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙበትን ሥልት በመቀየስና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት ይሰጣል። ከዚህም በተጨማሪ ቦርዱ የሥነ ዜጋና የመራጮች ትምህርት መስጠት እንዲችሉ ሕጋዊ ሰውነት ላላቸው የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶችና የትምህርት ተቋማት፤ የማስተማር ፈቃድ ይሰጣል። በዚህም መሠረት ቦርዱ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የመራጮች ትምህርት ለመስጠት ለሚፈልጉ የሲቪል ማኅበረሰብ ተቋማት ጥሪ ያቀረበ ሲሆን፤ በጥሪውም መሠረት ቦርዱ መሥፈርቱን አሟልተው ለቀረቡ 16 የመጀመሪያ ዙር የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ፈቃድ ሰጥቷል።

Share this post

በሕዝበ ውሳኔ ጥያቄ ዙርያ ክርክር/ውይይት ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው አካላት የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የምርጫ ቦርዱ በሕዝብ ውሣኔው ላይ በሚነሡ የተለያዩ ሃሳቦች ላይ የሚደረገውን ክርክር ለማስተባበር ይፈልጋል። በመሆኑም ቦርዱ በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት ያላችሁ ተቋማት እና መገናኛ ብዙኃንን በተናጠል ወይም በጋራ በመሆን ክርክር የማዘጋጀት ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ (Expression of interest) እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

ማንኛውም በህዝበ ውሳኔ ዙርያ ክርክር ወይም ውይይት ለማዘጋጀት የሚያስብ ተቋም የሚመለከቱትን ዋና ዋና ነገሮችን የያዘ የፍላጎት መግለጫ ሰነድ ሊያቀርብ ይገባል።

በሕዝበ ውሳኔ ጥያቄ ላይ በሚደረግ ክርክርና ውይይት ለመሳተፍ ፍላጎት ላላቸው የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ መሰረት የመራጮች የግል ውሳኔ በመረጃ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የሚያስችል በቂ መረጃ እና ሀሳብ እንዲያገኙ ለማድረግ ቦርዱ በህዝበ ውሳኔው አማራጮች ላይ ሃሳቦች እና አስተያየቶች ወደ ህዝብ የሚቀርብባቸውን የክርክር፣ የውይይት፣ እና የምከክር መድረኮችን በማመቻቸት ላይ ይገኛል።

በሕዝበ ውሳኔ ጥያቄ ላይ በሚደረግ ክርክርና ውይይት ለመሳተፍ ፍላጎት ላላቸው የተደረገ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ በተመለከተ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ እንደሆነ ይታወቃል። በዚህ መሰረት የመራጮች የግል ውሳኔ በመረጃ ላይ የተመሰረተ እንዲሆን የሚያስችል በቂ መረጃ እና ሀሳብ እንዲያገኙ ለማድረግ ቦርዱ በህዝበ ውሳኔው አማራጮች ላይ ሃሳቦች እና አስተያየቶች ወደ ህዝብ የሚቀርብባቸውን የክርክር፣ የውይይት፣ እና የምከክር መድረኮችን በማመቻቸት ላይ ይገኛል።