ቦርዱ ያዘጋጀውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋልን ለማዳበር የሚረዳ አውደ ጥናት ተካሄደ፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተባበሩት መንግሥታት የልማት ፕሮግራም (UNDP) ድጋፍ በአማካሪ ተቋም ያስጠናውን በ 2013 ዓ.ም. ሀገራዊ ምርጫ ወቅት ሢሠራበት የነበረውን የሥነ ዜጋና መራጮች ትምህርት ማስተማሪያ ማንዋል የሲቪል ማኅበራት ድርጅት አመራሮች፣ ተወካዮች፣ የቦርዱ የፌደራል እና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊዎች እና የስነ-ዜጋና አካታችነት ባለሙያዎች በተገኙበት በመገምገም ሰነዱን የሚያዳብሩ ጠቃሚ ግብዓቶችን ሰበሰበ።