የኢትዮጵያ ሕፃናት ፓርላማ ምርጫ ሪፖርት
ዓለም አቀፍ የልጆች ቀን ለታዳጊ ትውልድ የተሻለና አስተማማኝ ሁኔታ ለመፍጠር የሚያስፈልገውን ትምህርት የማግኘት፣ ከጤና ጥበቃ እንዲሁም ሕጻናቶች ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች እና መብቶች ጋር በተያያዘ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የሚረዳ መድረክ ሆኖ ያገለግላል። የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የልጆች ቀን ህዳር 11 ቀን 2017 ዓ.ም. በኢትዮጵያ ከተከበረባቸው ኩነቶች አንዱ የኢትዮጵያ ሕፃናትን ፓርላማን ምርጫ ማከናወን ነበር።