የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሜ የሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በወላይታ ዞን የሚደረገውን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ አስመልክቶ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትላንትናው ዕለት ሚያዚያ 26 ቀን 2015 ዓ.ም. ውይይት አካሄደ። የፌዴሬሽን ምክር ቤትና የሕዝብ ተወካዩች ቋሚ ኮሚቴ ተወካዩች፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች፣ የዞኑ አመራሮችና የፀጥታ አካላት እንዲሁም የፌደራል ፖሊስና የፍትሕ ሚኒስቴር ተወካዮች የተገኙበትን መድረክ በንግግር የከፈቱት የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ ሲሆኑ፤ በንግግራቸውም የመድረኩ ዋና ዐላማ በወላይታ ዞን የተደረገው ሕዝበ ውሣኔ ላይ ቀደም ሲል ያጋጠሙ የሕግ ጥሠቶች በድጋሚ እንዳይፈጠሩ አስቻይ ሁኔታዎችን በጋራ ለመፍጠር ታሳቢ እንዳደረገና ይህንንም ለማድረግ የመድረኩ ተሣታፊ የሆኑት ባለድርሻ አካላት ሚና ከፍተኛ እንደሆነ በማሰብ ጭምር እንደሆነ ተናግረዋል።