የ7ኛው ጠቅላላ ሀገር አቀፍ ምርጫ የዕቅድ ዝግጅት ምክክር ተጀመረ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ እና የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕቅድ ዝግጅት ላይ የቦርዱ ሥራ አመራር አባላት፣ የቦርዱ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎች በታደሙበት አውደ ጥናት አካሄደ።
የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕቅድን ከወዲሁ ማዘጋጀት ያስፈለገበት ዓላማ ምርጫውን ሕጉ በሚፈቅደው የምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ለማካሄድ ዕቅዱን ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመላክ ለምርጫ ማስፈፀሚያ ሥራው የታለመው በጀት በወቅቱ እንዲፀድቅ ለማስቻል ያለመ ነው።
የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት በ2018 ዓ.ም ለምናካሂደው የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዝርዝር፣ የሚለካ፣ ወጪ ቆጣቢ እና በጊዜ የተገደበ ብሎም ለእያንዳንዱ የምርጫ ተግባሮቻችን ምክንያታዊ እና ተጨባጭ በጀት ለማዘጋጀት ይህን አውደ ጥናት አዘጋጅተናል ብለዋል።