Skip to main content

የ7ኛው ጠቅላላ ሀገር አቀፍ ምርጫ የዕቅድ ዝግጅት ምክክር ተጀመረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ2018 በጀት ዓመት ዓመታዊ ዕቅድ እና የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕቅድ ዝግጅት ላይ የቦርዱ ሥራ አመራር አባላት፣ የቦርዱ ሥራ ክፍል ኃላፊዎችና የክልል ቅርንጫፍ ፅ/ቤት የሥራ ክፍል ኃላፊዎች በታደሙበት አውደ ጥናት አካሄደ።

የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዕቅድን ከወዲሁ ማዘጋጀት ያስፈለገበት ዓላማ ምርጫውን ሕጉ በሚፈቅደው የምርጫ የጊዜ ሠሌዳ ለማካሄድ ዕቅዱን ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በመላክ ለምርጫ ማስፈፀሚያ ሥራው የታለመው በጀት በወቅቱ እንዲፀድቅ ለማስቻል ያለመ ነው።

የቦርዱ ሰብሳቢ ወ/ሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ እንዳሉት በ2018 ዓ.ም ለምናካሂደው የ7ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ ዝርዝር፣ የሚለካ፣ ወጪ ቆጣቢ እና በጊዜ የተገደበ ብሎም ለእያንዳንዱ የምርጫ ተግባሮቻችን ምክንያታዊ እና ተጨባጭ በጀት ለማዘጋጀት ይህን አውደ ጥናት አዘጋጅተናል ብለዋል።

Share this post

ቦርዱ አካል ጉዳተኞች በቀጣይ ምርጫዎች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው የዳሰሳ ጥናት እያስጠና መሆኑ ተገለፀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አካል ጉዳተኞች በ6ኛው ጠቅላላ ሀገራዊ ምርጫ የነበራቸውን ተሳትፎና ውክልና ምን ይመስል እንደነበረ አማካሪ ድርጅት ቀጥሮ በማስጠናት ላይ ይገኛል።

የዳሰሳ ጥናቱ ዋነኛ ዓላማ እነዚህ የማህበረሰብ ክፍሎች የፓለቲካ ተሳትፎቸው ውስን እንዲሆን ያደረጓቸውን ችግሮች ነቅሶ በማውጣት በቀጣይ በሚኖሩ ምርጫዎች ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዲኖራቸው ቦርዱ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ሊተገብሯቸው የሚገቡ ምክረ ሃሳቦችን ለማመላከት ያለመ ነው።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በሶማሌ ክልል ውስጥ ለሚገኙ የአንደኛ እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ለከፍተኛ የትምህርት ተቋማት አስረከበ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል ዜጎች በዕዉቀት ላይ የተመሠረተ ምርጫን እንዲያደርጉ እና የዜግነት መብት እና ኃላፊነታቸውን በመገንዘብ ንቁ ተሳትፎ እንዲኖራቸው ያስችል ዘንድ ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ እና በምርጫ ሂደት ዙሪያ የተዘጋጁ የህትመት ውጤቶችን በድሬደዋ ከተማ አስተዳደር አሰራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን ለዜጎች ተደራሽ ከሚያርግባቸው ስልቶች መካከል የተለያዩ መረጃዎችን እና ትምህርቶችን ያያዙ የህትመት ውጤቶች ስርጭት አንደኛዉ መንገድ ነው፡፡ በዚህም መሠረት የቦርዱ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በቦርዱ የድሬደዋ አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል በድሬደዋ አስተዳደር ውስጥ ለሚገኙ የድሬደዋ ዩኒቨርሲቲ፣ የድሬደዋ አስተዳደር የሕዝብ ቤተ-መጻህፍት እና በከተማ እና በገጠር ለሚገኙ 28 የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ በአማርኛ፣ በኦሮምኛ ፤ እና በሶማልኛ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬል የተዘጋጁ አምስት የተለያዩ ይዘት ያላቸው ማለትም፤ ‘የምርጫ ሒደት’፣ ‘ምርጫ በኢትዮጵያ’፣ ‘ኢትዮጵያ ምን ዓይነት የምርጫ ሥርዓት ትከተላለች’ ፣’ ሰላማዊ ምርጫ በኢትዮጵያ’፣ እና ‘ዴሞክራሲ እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት’ በሚሉ ርዕሶች የተዘጋጁ በቁጥር 3530 ብሮሸሮች እና መጽሔቶችን አስረክቧል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ውጤቶችን በአፋር ክልል ውስጥ ለሚገኙ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች አሰራጨ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ስለምርጫ ሒደት እና የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ዜጎች በቂ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ የተለያዩ ስልቶችን በመቀየስ መልዕክቶችን ተደራሽ ማድረግ ላይ እየሠራ ይገኛል፡፡ በዚህም መሠረት የቦርዱ የሥነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ሥራ ክፍል በቦርዱ የአፋር ክልል ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል በአፋር ክልል ውስጥ ለሚገኙ የሰመራ፣ ሎግያ፣ አይሳ፣ ዱብቲ እና ሚሌ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች እንዲሁም አሳይታ መምህራን እና ሰመራ ጤና ሳይንስ ኮሌጆች በአማርኛ እና በአፋርኛ ቋንቋዎች የተዘጋጁ አምስት የተለያዩ ይዘት ያላቸው ማለትም፤ የምርጫ ሒደት፣ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ ኢትዮጵያ ምን ዓይነት የምርጫ ሥርዓት ትከተላለች፣ ሰላማዊ ምርጫ በኢትዮጵያ፣ እና ዴሞክራሲ እና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በሚሉ ርዕሶች የተዘጋጁ በቁጥር 11900 ብሮሸሮች እና መጽሔቶችን አስረክቧል፡፡

Share this post

ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች የምርጫ ተሳትፎ እንዲጎለብት እየሠራ ነው

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሁሉም የሀገራችን ዜጎች የፓለቲካ ተሳትፎ መብታቸው በተለይም የመመረጥና መምረጥ መብታቸው እንዲጎለብት አካታች የምርጫ ሥርዓትን ለማጠናከር ዘርፈ ብዙ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል።

ይህንንም ዕውን ለማድረግ ቦርዱ የሀገር ውስጥ ተፈናቃዮች በምርጫ ሂደት የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ያላቸውን ፍላጎት እና የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች በዳሰሳ ጥናት በመለየት ምቹ የምርጫ ከባቢ ለመፍጠር ኢስት አፍሪካ ከተባለ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር በአማካሪ ድርጅትነት ቀጥሮ በማስጠናት ላይ ይገኛል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለታቀደው የዳሰሳ ጥናት አማካሪ ድርጅቱ የጥናቱን መነሻ ዕቅድ ሪፖርት ለቦርዱ ሥራ አመራር፣ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች፣ ባለሙያዎች እንዲሁም ባለድርሻ አካላት በማቅረብ ዕቅዱን (Inception plan) የሚያጎለብቱ የሀሳብ ግብዓቶችን (ምክረ ሃሳቦችን) ሰብስቧል።

Share this post

የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ የመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል ቦርዱ ከባለድርሻ አካላት ጋር መከረ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሀገራችን የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ በተደገፈ ሥርዓት በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ታግዞ ለማዘመን እንቅስቃሴ ጀምሯል።

በመጀመሪያ ዙር የምርጫ ጣቢያዎችን በመልከዓ ምድር የመረጃ ሥርዓት (ጂ.አይ. ኤስ) ለማካለል የታቀደው ሥራ በድሬደዋ ሁለት፣ በሐረሪ ሶስት፣ በሲዳማ አስራ ዘጠኝ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ሰባት የምርጫ ክልሎች ላይ እንደሚተገበር ታውቋል።

ይህንንም ተከትሎ በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ኢትዮጵያ፤የሐረር እና የሲዳማ ክልሎች እና የድሬደዋ ከተማ አስተዳደር የክልል አስተዳደር አካላት፤ የሠላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች፤ የፖሊስ ኮሚሽነሮች እና የየክልሎቹ የምርጫ ላይዘን ኦፊሰሮች ታዳሚ ነበሩ::

Share this post