ቦርዱ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ በተያዘው ዓመት ለማካሄድ ልዩ ልዩ የቅድመ-ምርጫ ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል። ቦርዱ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም. የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ በማስመልከት ከፖለቲካ ፓርቲ አመራሮችና ተወካዮች ጋር ምክክር አድርጓል። ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳው የምርጫ ጽ/ቤቶችን ከማደራጀት ጀምሮ እስከ ይፋዊ የምርጫ ውጤት ማሳወቂያ ድረስ ያሉትን ተግባራት ያካተተ ነው።