የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከናይጄሪያ አቻው Independent National Electoral Commission (INEC) ጋር የልምድ ልውውጥ አደረገ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በቅድመ ምርጫ ተግባራቱ የምርጫ አፈጻጸምን ያዘምናሉ ያላቸውንና ነፃና ተዓማኒነቱን፤ አሣታፊና ተደራሽነቱን ለማጎልበት የሚያግዙትን በርካታ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚኽም ውስጥ በ6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለአፈጻጸም አስቸጋሪና ተግባራዊ ለማድረግ መሬት ላይ ካለው ተጨባጭ ሁነት ጋር መጣጣም ያልቻሉትን የሕግ ማዕቀፎች በባለሞያ አስጠንቶና ባለድርሻ አካላትን አማክሮ በማሻሻል ማፀደቅ፣ ተደራሽነቱንና አሣታፊነቱን ለማረጋገጥ የሚያግዙት ተጨማሪ ቅርንጫፍ ቢሮዎችን መክፈት፣ የምርጫ ጣቢያዎችን በቴክኖሎጂ ታግዞ በመመዝገብ ታዛቢዎችን ጨምሮ ለባለድርሻ አካላት በቀላሉ ለመለየት እንዲቻሉ የሚያስችል ሥራ መሥራት፣ ለምርጫና ለቢሮ ሥራ የሚያግዙ ቁሳቁሶችን ማሟላት እንዲሁን የቦርዱን ሠራተኞች ዐቅም የሚያጎለብቱ ሥልጠናዎችን በሀገር ውስጥና ከሀገር ውጪ እንዲወስዱ ማስቻል ተጠቃሽ ናቸው። ቦርዱ ከላይ ከተጠቀሱት ተግባራት በተጨማሪም ከተለያዩ ሀገራት የምርጫ ቦርድ ተቋማት ጋርም እን