ቦርዱ “የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት" የተሰኘው መርኅ-ግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን አካሄደ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ “የማኅበረሰብ ቲያትር ለአካታች የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት” የተሰኘ መርኅ ግብር በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በወላይታ ዞን አካሄደ። በተጠናቀቀው ግንቦት ወር 2017 ዓ.ም. ለተከታታይ ዘጠኝ ቀናት የተካሄደው መርሐ-ግብር ማስጀመሪያ በወላይታ ሶዶ ከተማ ሁለተኛ ደረጃ መሰናዶ ትምህርት ቤት የተካሄደ ሲሆን፤ በትምህርት ቤት ውስጥ ያሉትን ከ74 በላይ አካል ጉዳተኛ ተማሪዎች ከግምት ውስጥ በማስገባትም በሥነ-ሥርዓቱ ላይ አካታችነትን የሚያስተምረውን ቲያትር መስማት ለተሳናቸው ታዳሚያን በቀጥታ ተተርጉሞ ቀርቧል።