የኢትዯጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የህትመት ውጤቶችን ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ለሚገኙ የትምህርት ተቋማት አስረከበ!
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ስራ ክፍል ዜጎች በምርጫ ሒደት እና በዴሞክራሲ ስርዓት ግንባታ ዙሪያ ግንዛቤን ያገኙ ዘንድ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ትምህርቶች እና መረጃዎችን ተደራሽ ማድረግ ላይ እየሰራ ይገኛል። በዚህም መሰረት የስራ ክፍሉ በቦርዱ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በኩል በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል፤ ሆሣዕና ከተማ አሰተዳደር፣ ሀላባ ዞን፣ ሀድያ ዞን፣ ጉራጌ ዞን፣ ስልጤ ዞን እና፣ ከምባታ ዞን ውስጥ ለሚገኙ 30 የሁለተኛ ደረጃ እና መሠናዶ ትምህርት ቤቶች በአማርኛ ቋንቋ “ምርጫ በኢትዮጵያ” በሚል ርዕስ የተዘጋጁ በቁጥር 900 ቡክሌቶችን አስረክቧል።