Skip to main content

ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ተሾሙ

ከዚህ ቀደም ቦርዱን በሰብሳቢነት ሲመሩ የነበሩት ብርቱካን ሚደቅሳ ከነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን መልቀቃቸው ተከትሎ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው 9ኛ መደበኛ ጉባኤ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል፡፡

ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ ቀደም ብሎም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የጽሕፈት ቤት ኃላፊ በመሆን ከየካቲት 2012 ዓ.ም እስከ የካቲት 2015 ዓ.ም ማገልገላቸው ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከወዲሁ ለወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉ መልካም የሥራ ዘመን እንዲሆንላቸው ይመኛል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

ታህሣሥ 9 ቀን 2016 ዓ.ም.

Share this post

በስነ ዜጋ እና መራጮች ትምህርት ላይ ለሚሳተፉ የሲቪል ማህበራት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕገ መንግስቱ እና በአዋጅ ቁጥር 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሰረት የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ የሲቪል ማህበራት ፍቃድ ይሰጣል።

የስነ ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት አስፈላጊነት ዜጎች በምርጫ ለመሳተፍ እና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ ለማድረግ በሚወስኑት ውሳኔ ላይ ተፅዕኖው በግልፅ ይታያል፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃም ይህንን ግብ እውን ለማድረግ የሲቪል ማህበረሰብ ተሳትፎም አስፈላጊ ነው።

በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የክርክር መድረኮችን ለማዘጋጀት ፍላጎት ላላቸው ተቋማት የቀረበ ጥሪ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተማሪዎች እና ወጣቶች መካከል በስነዜጋ እና በዲሞክራሲያዊ ምርጫ እሳቤዎች ዙርያ የክርክር መድረኮችን ለማዘጋጀ ፍላጎት ላላቸው ተቋማት ጥሪ ያቀርባል።

በመሆኑም ከዚህ በፊት ጥያቄ/ ማብራሪያ ያስገባችሁም ሆነ በዚሁ ጉዳይ ላይ ፍላጎት ያላችሁ መንግስታዊ ያልሆናችሁ ተቋማት እና ሚዲያዎች በተናጠል ወይም በጋራ የምርጫ ክርክር ዝርዝር የፍላጎት መግለጫ ወረቀት (Expression of interest) ለቦርዱ እንድታቀርቡ ጥሪ ያቀርባል።

ማንኛውም ክርክር ለማከናወን የሚያስብ ተቋም የሚመለከቱትን ዋና ዋና ነገሮችን ያሟላ የፍላጎት መግለጫ ሊያቀርብ ይገባል።

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለክልል ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች የአቅም ግንባታ ሥልጠና ተሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ በሰራው የፍላጎት ዳሰሳ ግኝት ላይ ተመስርቶ ያዘጋጀውን አራተኛ ዙር ሥልጠና ለምርጫ ቦርዱ የክልል ቅርጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች “ምርጫ ነክ አለመግባባቶችን በምርጫ ሕጉ መሠረት በሚፈቱበት ሂደት፤ በአማራጭ የክርክር አፈታት ሂደቶች፤ በምርጫ ወቅት በሴቶች ላይ በሚደርሱ ጥቃቶች እና በስርዓተ ጾታ እና አካታችነት” ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ለሶስት ቀናት የቆየ የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጥቷል፡፡

ከኀዳር 26 እስከ ኀዳር 28 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ በቆየው ስልጠና ወደ 33 የሚደርሱ ከምርጫ ቦርድ የክልል ቅርጫፍ ጽ/ቤቶች የተውጣጡ የየቅርንጫፉ ጽ/ቤት ኃላፊዎች እና ሠራተኞች ተሳትፈዋል፡፡

ሥልጠናው ከምርጫ ቦርድ የሕግ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ጉዳዮች እና የስርዓተ ጾታ የሥራ ክፍሎች ባለሙያዎች እና ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ሲሆን በምርጫ ቦርድ የሥልጠና ሥራ ክፍል አስተባባሪነት እንዲሰጥ ተደርጓል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባለሙያዎች ዘመናዊ የሪከርድና መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ለመዘርጋት የሚያስችላቸውን ስልጠና ወሰዱ

በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለተውጣጡ ባለሙያዎች በዶክመንቴሽን፣ በሪከርድ እና መረጃ አስተዳደር ርዕሰ ጊዳዮች ላይ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት በመጡ የዘርፉ ባለሙያዎች አማካኝነት ከ ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጥቅምት 30 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ የቆየ ስልጠና ተሰጥቷል።

አስር ቀን በቆየው ስልጠና በቦርዱ የሥራ ሂደት የሚሰበሰቡ ሪከርዶች ታሪካዊ ፋይዳቸው የላቀ በመሆኑ ሳይንሳዊ በሆነ ዘመናዊ የሪከርዶች አስተዳደር ስርዓት መደራጀት እና መጠበቅ እንዳለባቸው አፅንዖት ተሰጥቶታል፡፡

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሥነ-ዜጋ ትምህርት እና በምርጫ ዙሪያ የተዘጋጁ የኅትመት ውጤቶችን በሕዝብ ቤተ-መጻሕፍትና በተለያዩ ተቋማት የማሠራጨት ሥራ አከናወነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ፤ በቦርዱ ማቋቋሚያ ዐዋጅ 1133/2011 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ጉዳዩ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመመካከር የሥነ-ዜጋ እና የመራጮች ትምህርት እንደሚሰጥ እና እንደሚያስተባብር ይታወቃል። ይህውም መራጮች በቂ ምርጫ ነክ ግንዛቤ የሚያገኙባቸውን የተለያዩ አማራጮች በመጠቀም ማለትም በኅትመት ውጤቶች (በበራሪ ወረቀቶች፣ በቡክሌት፣ በብሮሸሮች እና በሌሎች አማራጮች) ግንዛቤ የሚፈጥሩ መልዕክቶችን በማዘጋጀት በትምህርት ተቋማት፣ በቤተ-መጻሕፍት እንዲሁም በመንግሥታዊና መንግሥታዊ ባልሆኑ ተቋማት ውስጥ በማስቀመጥ ለዜጎች ተደራሽ የማድረግ ሥራ ይሠራል። ቦርዱ ከላይ የተጠቀሰውን ኃላፊነት ለመወጣት በቦርዱ የሥነ-ዜጋና የመራጮች ትምህርት ክፍል አማካኝነት የግንዛቤ መስጫ ኅትመቶቹን በተለያዩ ቋንቋዎች እንዲሁም በብሬልም ጭምር እያዘጋጀ በማሠራጨት ላይ ይገኛል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በወላይታ ዞን ሲያከናወን የቆየዉን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ውጤት የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ ጊዜያዊ ውጤት ይፋ አድርጓል

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በ1,812 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያስፈጸመውንና 849,896 መራጮች ድምፅ የሰጡበትን የወላይታ ዞን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ የውጤት ማዳመሩን ሥራ በዞኑ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሲያከናወን መቆየቱ ይታወቃል። በዛሬውም ዕለት ቦርዱ የውጤት የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።

ዝርዝር መግለጫዉን ለመመልከት እዚህ ላይ ይጫኑ

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በዎላይታ ዞን ለሚያስፈጽመው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ፣ የምርጫ አስፈጻሚዎች ወደ ዎላይታ ዞን የማጓጓዝ ሥራ ተጠናቀቀ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሁለት ቀናት በኋላ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በዎላይታ ዞን ለሚያስፈጽመው የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ ምርጫ የተለያዩ የቅድመ ምርጫ ተግባራትን በማከናወን ላይ መሆኑ ይታወቃል። ከነዚህም የቅድመ ምርጫ ተግባራት ውስጥ አንዱ ከአዲስ አበባ በመመልመል ያሠለጠናቸውን የምርጫ ጣቢያ አስፈጻሚዎች ከአዲስ አበባ የሕዝበ ውሣኔው ወደ’ሚካሄድበት ዎላይታ ዞን ውስጥ ወደ’ሚገኙ 1,804 ምርጫ ጣቢያዎች በሁለት ዙር ማጓጓዝ ይጠቀሳል። በዚህም ሰኔ 6 እና ሰኔ 8 ቀን 2015 ዓ.ም. በድምሩ 5215 አስፈጻሚዎች ወደ ዎላይታ ዞን የማጓጓዝ ሥራው ተጠናቋል።

Share this post