Skip to main content

የእጩዎች የመጨረሻ ዙር የማጣራት ሂደት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል ነገር ግን ስማችሁ ከዚህ በታች የተዘረዘረው ግለሰቦች በ 2013 ዓ.ም በ6ኛው ዙር ሀገራዊ ምርጫ ወቅት እጩ የነበራችሁ ሲሆን አሁን በምናደርገው ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ እንድትሳተፉ በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላችሁ ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካችሁ ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች አስከ ግንቦት 12 ቀን 2016 ዓ.ም. እስከ ጠዋቱ አራት ሰዓት ድረስ በስልክ ቁጥር 0995003794 በመደወል እንድታሳውቁ ቦርዱ ጥሪ ያቀርባል፡፡

Share this post

እጩ ከነበራችሁበት ፓርቲ መልቀቃችሁን ስለማሳወቅ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛውን ዙር ቀሪ እና ድጋሚ ምርጫ ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. እንደሚያከናውን ይታወቃል፡፡ ለዚህም ይረዳ ዘንድ የዕጩ ምዝገባ ከሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ስማችሁ ከዚህ በታች የተገለጹት የፓርቲያችሁ አባላት በዚህ ምርጫ እንደማይሳተፉ እና በሌላ እጩ መተካታቸውን አሳውቃችሁናል፡፡ ይሁን እንጂ ቦርዱ በምርጫ አዋጁ 1162/2011 አንቀጽ 39 (2) መሰረት የእጩዎችን የመወዳደር መብት ለመጠበቅ የመጨረሻ ማጣራት እያከናወነ ይገኛል፡፡

በመሆኑም ግለሰቦችን በቦርዱ የመረጃ ቋት ውስጥ ባላቸው ስልክ ቁጥር በመደወል ለማግኘት የተደረገው ጥረት ስልካቸው ሊሰራ ባለመቻሉ ምክንያት ሊሳካ አልቻለም። በዚህ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተዘረዘረው ግለሰቦች ከፖለቲካ ፓርቲያችሁ መልቀቃቸሁን ለፓርቲያችሁ እንድታሳውቁ እና መልቀቃችሁን የሚገልጽ ሰነድ ለቦርዱ እንድትልኩ እንጠይቃለን።

Share this post

ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ሰኔ 9 ቀን 2016 ዓ.ም. የሚካሄደውን ምርጫ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን የቀረበ ጥሪ

የመገናኛ ብዙኃን ቀጣዩ የ6ኛው ዙር የጠቅላላ እና የድጋሚ ምርጫ ባልተካሄደባቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ አፋር፣ ሶማሌ እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ምርጫው ፍትሐዊ፣ ገለልተኛና ተዓማኒ እንዲሆን የሚያበረክቱት ሚና ከፍተኛ መሆኑን በመገንዘብ፤ የመገናኛ ብዙኃኑና ጋዜጠኞች በምርጫ ጣቢያዎች ተገኝተው ለመዘገብ የሚያስችል የፍቃድ ጥያቄያቸውን ለቦርዱ እንዲያቀርቡ ይህንን ጥሪ ማድረግ አስፈልጓል፡፡ በዚህ መሠረት ለመዘገብ ጥያቄ የሚያቀርቡ የመገናኛ ብዙኃን፡

Share this post