በሶማሌ ብሔራዊ ክልል ስለሚደረገው የመራጮች ምዝገባ አቤቱታ ማጣራት የተሰጠ ማስታወሻ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚያዝያ 30 ቀን 2013 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው በሶማሌ ብሔራዊ ክልል የሚገኙ የተለያዩ የፓለቲካ ፓርቲዎች የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ ጉልህ የአሰራር እና የህግ ጥሰቶች አሉት በሚል አቤቱታ እና ማስረጃ ማቅረባቸውን፣ እንዲሁም የቀረቡት አቤቱታዎች እና ማስረጃዎች መሰረት አድርጎ ምርመራ ማድረግ እንደሚገባ ቦርዱ መገንዘቡን እና በዚህም መሰረት መጣራት እነደሚገባቸው በማመን በሰባት የምርጫ ክልሎች የመራጮች ምዝገባ በጊዜያዊነት እንዲቋረጥ በመወሰን የምዝገባ ሂደቱ ላይ የቀረቡ አቤቱታዎችን ማጣራት እንደሚያከናውን ማሳወቁ ይታወሳል።