የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለደ/ብ/ብ/ህ ክልል ፓሊስ ኮሚሽን የጻፈው ደብዳቤ

መድረኩን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የመሩት ሲሆን፤ ምርጫ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን የሚያሣትፍ መድረክ እንደሆነና ከባለድርሻ አካላቱ መካከልም ፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ እንደመሆናቸው መጠን ስሕተቱንም ስኬቱንም እንዲያውቁ በማድረግ እየተራረሙ ለመሄድ በተከታታይ እየተዘጋጁ ያሉት መድረኮችን ማዘጋጀት እንዳስፈለገ ገልጸዋል። የሰብሳቢዋን ንግግር ተከትሎ የቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረቦች ለምርጫ ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች የግዢ አፈጻጸም፤ ሥርጭትና የሰው ኃይል ሥምሪትን፣ የቁሳቁሶች ጥራትና ደኅንነት አጠባበቅን፣ እንዲሁም ከምርጫ ጣቢያዎች አከፋፈት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት ቀናት ማለትም የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. እና የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. 6ኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ማመልከቻ ላስገቡ እና በመጀመሪያ ዙር ላለፉ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሥልጠና ሰጠ። በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ የተከፈተው መድረክ የተለያዩ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ በቦርዱ የፕሮግራም ባለሙያ-የውጭ ግንኙነት ክፍል፣ በቦርዱ የሥርዓተ -ፆታ እና አካታችነት ክፍል እንዲሁም ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮ ባላቸው ባለሙያ ቀርቧል። ሥልጠናውን ለምን መስጠት እንዳስፈለገ የተናገሩት የቦርድ አመራሯ ብዙወርቅ ከተተ፤ የተወሠኑት ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ያስገቡት ሠነድ ላይ የዕቅድ አወጣጥና ዘዴ ክፍተት በመታየቱ እንደሆነ ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 21 ቀን 2013 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 17 ቀን 2013 ዓ.ም. እና መጋቢት 18 ቀን 2013 ዓ.ም.
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ለመራጮች ምዝገባ ያለውን የቁሳቁስ ዝግጅት ለብዙኃን መገናኛ አካላት አስጎበኘ። በቦሌ ዐየር ማረፊያ ካርጎ በሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ መጋዘን በመከናወን ላይ ያለውን አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሥራ ምን እንደሚመስል ማስተዋወቅ ዐላማው ያደረገው ጉብኝት፤ በቦርዱ የኮሚኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ገለጻ የተጀመረ ሲሆን፤ ኃላፊዋ ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ያለውን አጠቃላይ ዝግጁነት የሎጂስቲክና የሎጂስቲክ ሥርጭት ዕቅድ አወጣጡን ጨምረው አብራርተዋል።
የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በአቶ አራርሶ ቢቂላ በተጻፈ ደብዳቤ ሁለተኛውን ጠቅላላ ጉባዔ መጋቢት 4 ቀን 2013 ዓ.ም. አካሂዶ መተዳደሪያ ደንቡን ማሻሻሉን፣ የፓርቲውንም ብሔራዊ ምክር ቤት መምረጡን እንዲሁም በማግስቱ መጋቢት 5 ቀን 2013 ዓ.ም. የድርጅቱን ብሔራዊ ምክር ቤት ተሰብስቦ የፓርቲውን ከፍተኛ አመራሮች መምረጡን ያስረዳሉ የተባሉ ሠነዶች በዛሬው እለት መጋቢት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስገባ ሲሆን ቦርዱ ለወደፊት እነዚህን ሰነዶች የሚመረምር እና አስፈላጊውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን ይገልጻል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም የካቲት 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ.ም ለመራጮች ምዝገባ የአሠልጣኞች ሥልጠና መስጠቱ ይታወሳል። የአሠልጣኞች ሥልጠናው ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለዞን አስተባባሪዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና ለልዮ ምርጫ ጣቢያ ሠራተኞች እንዲሁም ለመሥክ አሠልጣኞች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የነበረ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞቹ ደግሞ መጋቢት 4 እና 5 ቀን 2013 ዓ.ም ሥልጠናው ተሰጥቷል።