Skip to main content

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የመረጮች ምዝገባና አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሂደቶችን ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን አስመልክቶ ለተወዳዳሪ ፓርቲዎች ሪፓርት አቀረበ

መድረኩን የቦርዱ ዋና ሰብሳቢ ብርቱካን ሚደቅሳ የመሩት ሲሆን፤ ምርጫ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን የሚያሣትፍ መድረክ እንደሆነና ከባለድርሻ አካላቱ መካከልም ፖለቲካ ፓርቲዎች አንዱ እንደመሆናቸው መጠን ስሕተቱንም ስኬቱንም እንዲያውቁ በማድረግ እየተራረሙ ለመሄድ በተከታታይ እየተዘጋጁ ያሉት መድረኮችን ማዘጋጀት እንዳስፈለገ ገልጸዋል። የሰብሳቢዋን ንግግር ተከትሎ የቦርዱ የኦፕሬሽን ክፍል ባልደረቦች ለምርጫ ምዝገባ የሚውሉ ቁሳቁሶች የግዢ አፈጻጸም፤ ሥርጭትና የሰው ኃይል ሥምሪትን፣ የቁሳቁሶች ጥራትና ደኅንነት አጠባበቅን፣ እንዲሁም ከምርጫ ጣቢያዎች አከፋፈት ጋር የተያያዙ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያዎችን ሰጥተዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ማመልከቻ ላስገቡ እና በመጀመሪያ ዙር ላለፉ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሥልጠና ሰጠ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለሁለት ቀናት ማለትም የካቲት 26 ቀን 2013 ዓ.ም. እና የካቲት 29 ቀን 2013 ዓ.ም. 6ኛውን አጠቃላይ ምርጫ ለመታዘብ ማመልከቻ ላስገቡ እና በመጀመሪያ ዙር ላለፉ ሀገር በቀል የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ሥልጠና ሰጠ። በቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ውብሸት አየለ የተከፈተው መድረክ የተለያዩ ክፍሎች ያሉት ሲሆን፤ በቦርዱ የፕሮግራም ባለሙያ-የውጭ ግንኙነት ክፍል፣ በቦርዱ የሥርዓተ -ፆታ እና አካታችነት ክፍል እንዲሁም ዓለም ዐቀፍ ተሞክሮ ባላቸው ባለሙያ ቀርቧል። ሥልጠናውን ለምን መስጠት እንዳስፈለገ የተናገሩት የቦርድ አመራሯ ብዙወርቅ ከተተ፤ የተወሠኑት ሲቪል ማኅበራት ድርጅቶች ያስገቡት ሠነድ ላይ የዕቅድ አወጣጥና ዘዴ ክፍተት በመታየቱ እንደሆነ ገልጸዋል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ ያለውን የቁሳቁስ ዝግጅት አስጎበኘ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መጋቢት 14 ቀን 2013 ዓ.ም. ለመራጮች ምዝገባ ያለውን የቁሳቁስ ዝግጅት ለብዙኃን መገናኛ አካላት አስጎበኘ። በቦሌ ዐየር ማረፊያ ካርጎ በሚገኘው የቦርዱ ጊዜያዊ መጋዘን በመከናወን ላይ ያለውን አጠቃላይ የኦፕሬሽን ሥራ ምን እንደሚመስል ማስተዋወቅ ዐላማው ያደረገው ጉብኝት፤ በቦርዱ የኮሚኒኬሽን ክፍል ኃላፊ ገለጻ የተጀመረ ሲሆን፤ ኃላፊዋ ቦርዱ ለመራጮች ምዝገባ ያለውን አጠቃላይ ዝግጁነት የሎጂስቲክና የሎጂስቲክ ሥርጭት ዕቅድ አወጣጡን ጨምረው አብራርተዋል።

Share this post

አጭር መረጃ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኦሮሞ ነፃነት ግንባር በአቶ አራርሶ ቢቂላ በተጻፈ ደብዳቤ ሁለተኛውን ጠቅላላ ጉባዔ መጋቢት 4 ቀን 2013 ዓ.ም. አካሂዶ መተዳደሪያ ደንቡን ማሻሻሉን፣ የፓርቲውንም ብሔራዊ ምክር ቤት መምረጡን እንዲሁም በማግስቱ መጋቢት 5 ቀን 2013 ዓ.ም. የድርጅቱን ብሔራዊ ምክር ቤት ተሰብስቦ የፓርቲውን ከፍተኛ አመራሮች መምረጡን ያስረዳሉ የተባሉ ሠነዶች በዛሬው እለት መጋቢት 13 ቀን 2013 ዓ.ም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ያስገባ ሲሆን ቦርዱ ለወደፊት እነዚህን ሰነዶች የሚመረምር እና አስፈላጊውን ውሳኔ የሚሰጥ መሆኑን ይገልጻል።

Share this post

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለመራጮች ምዝገባ ስልጠናዎችን አከናወነ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሁለት ተከታታይ ቀናት ማለትም የካቲት 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ.ም ለመራጮች ምዝገባ የአሠልጣኞች ሥልጠና መስጠቱ ይታወሳል። የአሠልጣኞች ሥልጠናው ለምርጫ ክልል ኃላፊዎች፣ ለዞን አስተባባሪዎች፣ ለምርጫ ጣቢያ ሠራተኞችና ለልዮ ምርጫ ጣቢያ ሠራተኞች እንዲሁም ለመሥክ አሠልጣኞች ለመስጠት የታቀደው ሥልጠና አካል የነበረ ሲሆን፤ ለመሥክ አሠልጣኞቹ ደግሞ መጋቢት 4 እና 5 ቀን 2013 ዓ.ም ሥልጠናው ተሰጥቷል።

Share this post