የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ 6ተኛ አጠቃላይ ምርጫን የተሻለ ግልጽነት እና ተአማኒነት አንዲኖረው ለማድረግ የተለያዩ ጥረቶች ሲያደርግ እንደቆየ ይታወሳል። ከዚህም መካከል ለፖለቲካ ፓርቲዎች የምርጫ አስፈጻሚዎችን ዝርዝር በመስጠት የገለልተኝነት ማጣራት እንዲያከናውኑ እና ለቦርዱ እንዲያሳወቁ ማድረግ አንዱ ነው።

በዚህ መሰረት ከዚህ በፊት በተለያዩ ዙሮች የምርጫ አስፈጻሚዎችን ዝርዝር ለፖለቲካ ፓርቲዎች እንዳቀረበ ይታወሳል፣ በመሆኑም በአሁኑ ወቅት ቦርዱ በተለያየ መልኩ የመለመላቸው እና ለመራጮች ምዝገባ ተግባር ላይ ሊሳተፉ የሚችሉ አስፈጻሚዎች ዝርዝርን አዘጋጅቷል። በመሆኑም ፓርቲዎች ከቦርዱ የተሰጣችሁን ፍላሽ ይዛችሁ በመምጣት ከፖለቲካ ፓርቲዎች የስራ ክፍል መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የመራጮች ምዝገባ ከሚጀመርበት ቀን አስቀድሞ (እስከ መጋቢት 15) አስተያየታችሁን ለቦርዱ እንድታቀርቡ እንጠይቃለን።

መጋቢት 2 ቀን 2013 ዓ.ም