የፖለቲካ ፓርቲዎች 6ተኛው አገራዊ ምርጫ እጩዎቻቸሁን እያስመዘገባችሁ እንደሆነ ይታወቃል። የእጩ ተወዳዳሪዎች ምዝገባ፣ የድጋፍ ፊርማ አሰባሰብ እና መለያ ምልክት አመራረጥ መመሪያ ቁጥር 07/2013 አንቀጽ 19 መሰረት እጩዎች ምዝገባ በምርጫ ክልል የሚከናወን ሲሆን የእጩዎች አጠቃላይ ዝርዝር ደሞ ለቦርዱ ይቀርባል።

በዚህም መሰረት የእጩዎች ዝርዝር መረጃን በእጩዎች ዝርዝር ማቅረቢያ ቅጽ በመጠቀም የምዝገባ የጊዜ ሰሌዳ ከመጠናቀቁ በፊት እንድታቀርቡ ቦርዱ ያሳሰባል።

ቅጹ ከቦርዱ ድረገጽ (ከስር በሚገኘው ሊንክ) እንዲሁም የፓለቲካ ፓርቲ የስራ ክፍል ማግኘት የሚቻል ሲሆን የሚከተሉትን ዝርዝሮች መያዝ አለበት።

.

የእጩ ስም ከነአያት

የእጩ ስራ

የሚወዳደርበት/የምትወዳደርበት ክልል/የከተማ መስተዳድር

የሚወዳደርበት/የምትወዳደርበት የምርጫ ክልል

የሚወዳደርበት/የምትወዳደርበት የምርጫ አይነት

የእጩዎች ዝርዝር ሰነዱ የፓርቲውን ስም፣ የፓርቲውን ሃላፊ ስምና ፊርማ እንዲሁም የፓርቲውን ማህተም መያዝ ይኖርበታል።

የካቲት 22 ቀን 2013 ዓ.ም