የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከሐበጋር ዲቤትስ ጋር በመተባበር በሐረር ከተማ የክርክር መድረኮችን አዘጋጀ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ዜጎች በመረጃ ላይ የተመሰረተ ምርጫ እንዲያደርጉ እና የዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ግንባታ ላይ የሚኖራቸዉን ተሳትፎ ለማጉላት የተለያዩ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎችን እየሠራ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ቦርዱ ከሐበጋር ዲቤትስ (ደበበ ኃ/ገብርኤል የሕግ ቢሮ) ጋር በመተባበር በሐረር ኤስ ኦ ኤስ እና በሐረር ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች በተማሪዎች መካከል የክርክር መድረክ አካሄዷል፡፡
የክርክሩ ፍሬ ሀሳቦች በሁለት ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ያተኮሩ ሲሆን እነርሱም፡ ለኢትዮጵያ የሚሻለዉ የፖለቲካ ሥርዓት ፕሬዝዳንታዊ ወይስ ፓርላሜንታዊ እንዲሁም የነፃ ገበያ ሥርዓት ለኢትዮጵያ ዕድገት የተሻለ ሥርዓት ነዉ ወይስ አይደለም? የሚሉ ነበሩ፡፡