ማሳሰቢያ: በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ መዘገብ ለምትፈልጉ መገናኛ ብዙኃን አካላት
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብ/ብ/ሕ ክልል በሚገኙ ስድስት ዞኖችና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም በጋሞ፣ ጎፋ፣ ወላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጌዲዮ እና ኮንሶ ዞኖች እንዲሁም ቡርጂ፣ ደራሼ፣ ባስኬቶ፣ አሌ እና አማሮ ልዩ ወረዳዎች ላይ የሚካሄደውን ሕዝበ ውሣኔ መዘገብ ለምትፈልጉ የመገናኛ ብዙኃን አካላት ጥቅምት 21 ቀን 2015 ዓ.ም. የምዝገባ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በዚህም መሠረት የ6ኛው ሀገራዊ ምርጫን ለመዘገብ ከቦርዱ የዕውቅና ባጅ ያገኙ የመገናኛ ብዙኃን አካላት፤ ሀገራዊ ምርጫውን ለመዘገብ የተሰጣቸው ባጅ ጥር 30 ቀን 2015 ዓ.ም. ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች ላይ በሚካሄደው ሕዝበ ውሣኔ ጥቅም ላይ መዋል የማይችልና አገልግሎቱ ያበቃ መሆኑን በመገንዘብ እንደገና ማመልከት እንደሚጠበቅባቸው ቦርዱ ያሳውቃል።