የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የተለያዩ የህትመት ዉጤቶችን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ አስረከበ
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በሕግ ከተሰጡት ኃላፊነቶች መሀከል መራጮች በቂ የምርጫ ነክ መረጃ እና ግንዛቤ የሚያገኙበትን አካታች ስልት መቀየስ እና የተለያዩ የመገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን መስጠት አንዱ ነዉ፡፡ በዚህም መሰረት የስነ-ዜጋ እና መራጮች ትምህርትን ለአካል ጉዳተኛ ማህበረሰቦች በቋሚነት ተደራሽ ለማድረግ በስፋት እየሠራ ይገኛል፡፡ይህንን ተከትሎ ግንቦት 27 ቀን 2016 ዓ.ም የተለያዩ በብሬል የተዘጋጁ የህትመት ዉጤቶችን፣ ማለትም ምርጫ በኢትዮጵያ በሚል ርዕስ የተዘጋጂ ቡክሌቶች፣ እንዲሁም የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና ስነምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011 አዋጆችን ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኬኔዲ እና ሕግ ላይብረሪ ክፍል አስረክቧል፡፡